TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ትዝብት‼️

በተወሰነ መልኩ ኢትዮጵያ ውስጥ መተው የሚሰሩ #ቻይና_የኮንስትራክሽን_ድርጅት በአገራችን ሰራተኞች ላይ የሚያሳዩት #ንቀት እና ዝቅተኛ የክፍያ መጠን የተወሰነ ፅፈህ ነበር።

እኔም ይህን አሳብ እጋራለው። እነኚህ ቻይኖች ህዝቡ ከሚያወራው የስራቸው ጥራት ማነስ እና መንግስት ያስቀመጣቸውን ተቆጣጣሪዎችን በሙስና ማጨማለቅ ውጪ ደግሞ የሰራተኛ ክፍያ አነስተኛ መሆን፣ የሰራተኛ አያያዝ ፣የሰራኛ የመብት ጥሰት፣ የሰራተኛ አስተነጋገድ ሁኔታ፣የደሞዝ ክፍያ ሰሌዳ፣ ስራ ላይ የተጎዳን (በስራ ቦታ የተጎዳ)፣ ሰራተኛን አያያዝ፣ሰራተኛ ሲቀነስ ወይም ሲቀነስ የሚከፈል አገልግሎት ክፍያ መከልከል በተጨማሪ ንዑስ ተቋራጮች (sub contractor) አያያዝ፣ አከፋፈል፣ የስራ አለካክ ላይ በጣም ችግር አለ!!!

እኔ sub contractor ነኝ ምሰራው ሀዋሳ ጩኮ መንገድ ስራ ላይ ነው። ይህን የሚሰራው sino hydro የኮንስትራክሽን ድርጅት መንገድ ስራውን የያዘው። ይህ ድርጅት ከላይ ከጠቁስክልህ ችግር ውጪ ሚሰራውን መንገድ ስራ በሚሰራበት ወቅት በጣም መንገድ ለመንገዱ የሚጎዳ በጣም አፀያፊ ስራ እየሰሩ ነው።

ለምሳሌ፦

1. ከዚህ በፊት የነበረውን ተነሺ አስፋልት ያነሱ እና እንደ ውሉ መጣል ነበረበት እነሱ ከዚህ በፊት የተነሳውን አስፋልት ከአዲስ ጋር ደባልቀው አስፋልቱን እየሰሩ ነው።

2. የመሬት ስራው በሚሰራበት ወቅት የመሬት ስራው ቆረጣ አለው። አላስፈላጊ የሆነውን የተቆፈረውን አፈር እንደ መጣለል Re use ነው ሚያረጉት። ይህ አስፋልት ከዚህ በፊት በህንዶች የመንገድ ስራ ተቋራጮች ተይዞ የነበረ መንገድ ስራ ነበር ነገር ግን ስንት ያገሬ ንብረት ወጥቶበት በጥራት ምክንያት ህንዶቹን ተባረዋል። ከዚያም እነኚህ የመጡት።

3. የአስፈልቱ ውፍረት እንደሰማነው 5 ሳሜ ነው። ፀግሽ ታምነኛለህ 3 ሳሜ ውፍረት ያለው አስፋልት የተሰራ እጅግ በጣም ብዙ ነው።

4. አስፋልት ከመሰራቱ በፊት የነበረው የመሬት ስራ በግርድፉ ሲታይ ሁለት ነገር አለው። አንደኛ sub base እና base course። ሰብ ቤዙ እንዳልኩ አንዳንድ ቦታ የተቆፈረውን መልሰው ይጠቀማሉ። ይህ ደግሞ ለአስፋልቱ መሰረት ስለሆነ ይህ sub base ደረጃ ሚጠብቀው ስላልሆነ የላይኛውን አስፋልት እድሜ እንዳይኖረው ዋነኛ ምክንያት ነው። ሁለተኛው base course ደግሞ ተመርጦ የመጣውን የአፈር አይነት ካለቀ ቡኃላ የሚደረግ የተቀመመ የተፈጨ የጠጠር አይነት ነው። ይህ ጠጠር በትንሹ ውፍረት ከ 30 ሳሜ ማነስ የለበትም። ቻይኖቹ መንገዱን ሲሰሩት ከስር የሚደረገውን አፈር ከመጠን በላይ ያደርጉ የምትደረገውን የጠጠር ውፍረት ከ10–20 ሳሜ ያደርጉት እና ማውጣት ያለባቸውን ሳያወጡ አገራችንን "ድህነት" ላይ ጥለው የተከለከለ ወንጅል ትርፍ ያጋብዛሉ።

ይህ ሁሉ ሲሆን ማንም ምንም አላለም ልትል ትችላለህ። ለሆዳቸው ያላደሩ ተቆጣጣሪዎች ባለሙያተኞች አሉ ነገር ግን እነኚህ ሰዎች ቻይኖቹ ከጣሊያናዊው ሽማግሌ ተቆጣጣሪ ጋር በመመሳጠር ባለው መብት ተጥቅሞ ተባረዋል። እነኚህ ሰዎች ሰሚ ቢያገኙ ሊናዘዙ ይችላሉ። ፀግሽዬ ከተጨመረው ውጪ መንገዱ የተያዘው በ44 USD ነው። በኛ ምን ያህል እንደሚመጣ ላንተ ልትወውና ይሄ ብር መንገስት በዚህ የዶላር ህጥረት ለስንት ችግሩ ማስታገሻ ያደርገው ነበር!!!
አደራ አደራ አደራ ፀግሽ ለሚመለከተው!!

@tsegabwolde @tikvahethiopia