TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በአዲስ አበባ ዙሪያ እየተካሄደ ካለው ቤት የማፍረስ ዘመቻ ጋር በተያያዘ ቤታቸው የፈረሰባቸው ግለሰቦች ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ ቅሬታ አቅርበው ነበር።

በዚህ መሰረትም የጉባኤው 3 የሰብዓዊ መብቶች ባለሞያዎች እና አንድ ሹፌር ታህሳስ 27 " ዓለም ባንክ " አካባቢ ጥቆማውን ለማጣራት ይሄዳሉ ፤ በፖሊስም ተይዘው ያሉበትን ማወቅ ሳይቻል ከቆየ በኃላ በተደጋጋሚ በተደረገ ጥረት አራቱም ሰራተኞችና የድርጅቱ መኪና ዓለምገና ሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደሚገኙ ታውቋል።

በተጨማሪም ፤ ኢሰመጉ ባሉት ባለሙያዎች ላይ የተለያዩ #ጫናዎች፣ $ዛቻ እና #ማስፈራራትን ጨምሮ እየደረሰበት እንደሚገኝ አሳውቋል።

ኢሰመጉ ይህ አይነት ድርጊት ከህግ አግባብ ውጭ የሆነና ጉባኤው የተቋቋመበትን ዓላማ (ለሰብዓዊ መብት መከበር) እንዳያስፈፅም እንቅፋት የሚሆንና ባለሞያዎቹ በነፃነት ተንቀሳቅሰው እንዳይሰሩ ለማድረግና #ለማሸማቀቅ የተደረገ ነው ብሎታል።

መንግስት በኢስመጉ ላይ የተለያየ አይነት #ህገወጥ_እስር እና የተለያዩ ጫናዎችን ከመፈፀም ይቆጠብ ያለው ጉባኤው ፖሊስ ሰራተኞቹን #በአስቸኳይ ከእስር እንዲፈታ አሳስቧል።

@tikvahethiopia