TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ፌደራል ፖሊስ⬇️

ለኦነግ አባላትና አመራር በአዲስ አበባ የተዘጋጀው የአቀባበል ስነስርዓት #ያለአንዳች ችግር መጠናቀቁን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል አስታወቁ።

ኮሚሸነሩ ከfbc ጋር ባደረጉት ቆይታ በአቀባበል ስነስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የሀገር መከላከያ፣ የኦሮሚያ ፖሊስ፣ የፌደራል ፖሊስ እና ደህንነት የተጠናከረ ጥበቃ ሲያደርጉ መቆየታቸውንም አንስተዋል።

በአቀባበል ስነስርቱ ላይ ከአራት ሚሊየን (4,000,000) #በላይ ህዝብ የተገኘ ሲሆን፥ የህዝቡን ሰላም በጠበቀ መልኩ #በሰላም መጠናቀቁን ገልጸዋል።

በአቀባበል ስነስርዓቱ ላይ የተገኙ #ወጣቶችም ከፖሊስ ጋር #ትብብር ሲያደርጉ መቆየታቸውን ያነሱት ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ #ጸጥታውን ለማስከበርም በጋር ሲፈትሹ እንደነበረም ጠቅሰዋል።

በዚህም #ቄሮዎችን ያመሰገኑ ሲሆን፥ ለሌሎችም አርአያ የሚሆን ተግባር መፈጸማቸውን ጠቅሰዋል።

የአዲስ አበባ ወጣትም የአቀባበል ስነስርዓቱ መጠናቀቅን ተከትሎ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች የሚመለሱ ወጣቶችን #ምግብና ውሃ በማዘጋጀት ግብዣ ሲያካሂድ እንደነበረ ገልጸዋል።

ኮሚሽነሩ ይህ #አንድነትን ይበልጥ የሚያጠናክርና ለሀገሪቱም ትልቅ #ተስፋ መሆኑን አንስተዋል።

አንዳንድ ቦታዎች ላይ "ወጣት ነን" የሚሉ ግለሰቦች #ድንጋይ የመወርወር አዝማሚያ ማሳየታቸውን የጠቀሱ ሲሆን፥ ፖሊስም #በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸው ተናግረዋል።

በተመሳሳይ በአዲስ አበባ #ዙሪያ በቄሮ ስም #የሚነግዱ ቄሮ ያልሆኑ ከአቀባበል ስነ ስርዓቱ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ግለሰቦች ዝርፊያና #ግድያ መፈጸማቸውን አንስተዋል።

በዚህም ፌደራል ፖሊስ፣ የኦሮሚያ ፖሊስ እና የሀገር መከላከያ ወደ አካባቢው በመሄድ ግለሰቦቹን በቁጥጥር ስር እያዋለ ይገኛል ብለዋል።

በጥቅሉ አቀባበሉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት የታየበት ጥሩ መንፈስ የነፈሰበት ህዝቡ እንግዶቹን ተቀብሎ በሰላም እንዲጠናቀቅ ያደረገበት ነው ብለዋል።

የአቀባበል ስነስርዓቱ በሰላም መጠናቀቅ ህዝቡ ላደረገው ትብብር፣ ለቄሮ እና ለአዲስ አበባ ህዝብ ምስጋና አቅርበዋል።

በአቀባበል ስነስርዓቱ ላይ የነበሩ ቄሮዎች ባሳዩት ትብብር ፖሊስ መኩራቱን ገልጸው በቀጣይም ፖሊስ ጋር በመሆን እጅና ጓንት ሆነው እንደሚሰሩ እምነታቸውን ገልፀዋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ🔝

ዛሬ ጥዋት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ(ማራኪ ካምፓስ) ተማሪዎች ሰልፍ አድርገው የነበር ሲሆን ሰልፉ ግቢውን ውጥረት ውስጥ ከቶት መጠነኛ አለመረጋጋት ተፈጥሮ ነበር። ተማሪዎች #ድንጋይ ሲወራወሩም እንደነበር የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ገልፀዋል። አሁን ላይ ዩኒቨርሲቲው የተአጋጋ ሲሆን ተማሪው ሰላማዊ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል። ተማሪዎች የካፌ አገልግሎት እየተጠቀሙ ናቸው።
.
.
TIKVAH-ETH ለሁሉም እንዲህ ይላል፦

ሰላም ዋጋዋ ትልቅ ነው!! አስተውሉ!! አስተውሉ!! ምንም ነገር ከሰላም አይበልጥም። በኃላ ደም እንባ ብናለቅስ ሰላምን መልሰን አናገኝም!!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሊታረም ይገባል‼️ዩኒቨርሲቲዎች የእውቀት ስፍራ ናቸው። ለሀገር ለውጥ ትልቁን ድርሻ በሚወስዱት ተቋማት ውስጥ ሆኖ #ዱላ መያዝ እና #ድንጋይ መወራወር ብሎም እርስ በእርስ መጋጨት ተገቢ አይደለም።

ይታረም‼️
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀላባ ከተማ ይቅርታ ጠየቀ🔝

ባሳለፍነው እሁድ በ6ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ሀላባ ከተማ በሜዳው ኢትዮጵያ መድንን ያስተናገደበት ጨዋታ በ76ኛው ደቂቃ ላይ ከተመልካች በተወረወረ #ድንጋይ የመሐል ዳኛው #ኤፍሬም_ደበሌ ላይ ጉዳት በመድረሱ ምክንያት መቋረጡ የሚታወስ ነው። ይህንን አስመልክቶም የሀላባ ከተማ ክለብ ለፌዴሬሽኑ የይቅርታ ደብዳቤ አስገብቷል።

የክለቡ ፕሬዝዳንት አቶ አንዋር ሲራጅ ስለ ጉዳዩ ለሶከር ኢትዮጵያ በሰጡት አስተያየት በተፈጠረው ስርዓት አልበኝነት በጣም እንዳዘኑ ገልፀው የሀላባ ከተማ በእግርኳስ ውድድሮች ባለፉት 10 ዓመታት ሲሳተፍ እንዲህ አይነት ድርጊት ታይቶ እንደማይታወቅ በማውሳት ከጨዋታው መቋረጥ በኋላ አመራሩ እንዲሁም የከተማው አስተዳደር ማምሻውን ስብስባ አድርጎ ወደ እርምጃ በመግባት ሁለት ተጠርጣሪዎችን ወዲያው በመያዝ በቀጣዩ ቀንም 9 ወጣቶችን በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ለፍርድ ለማቅረብ ምርመራ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልፀዋል። 

ፕሬዝዳንቱ የሀላባ እግር ኳስ ክለብ እና የከተማው አስተዳደር የተፈጠረውን ሁሉ አጥብቆ እንደሚቃወምና እንዲህ አይነት ድርጊት ዳግም እንዳይፈፀም አጥብቀው እንደሚሰሩ በመግለፅ የሚመለከታቸው አካላትን በክለቡ እና በሀላባ ህዝብና አስተዳደር ስም ይቅርታ መጠየቀቸውን ለሶከር ኢትዮጽያ ገልፀዋል።

ምንጭ፦ ሶከር ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ገዳዮች ለፍርድ መቅረብ አለባቸው " ከሰሞኑን የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ያሳለፈው አዲስ አደረጃጀት በጉጂ ዞን በተለያዩ ቦታዎች ተቃውሞ እንደገጠመው የቲክቫህ አባላት ከየአካባቢው አሳውቀዋል። ትላንት ከዚህ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ በቦሬ ማቲ በፀጥታ ኃይሎች በተወሰደ የኃይል እርምጃ የሰው ህይወት ስለመጥፋቱ ተሰምቷል። አንድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል " መንግስት በሰላማዊ ተቃውሞ…
" ሠልፉ ያልተፈቀደ ነበር " - የቦሬ ሰላምና ፀጥታ ጽሕፈት ቤት

ትላንት በኦሮሚያ ክልል፣ ጉጂ ዞን ቦሬ ከተማ ከተቃውሞ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ 3 ሰዎች በፀጥታ ኃይሎች መገደላቸው መግለፁ ይታወሳል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የቦሬ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽሕፈት ቤት ዛሬ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ በሰጠው ቃል ፤ ትላንት በከተማው ስለደረሰው ጉዳት ማረጋገጫ ሰጥቷል።

የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ቡሌ ትናንት በከተማው በተካሄደው ሠልፍ ጉዳት መድረሱን አረጋግጠው " ሠልፉ ያልተፈቀደ " እንደነበር ገልጸዋል።

ኃላፊው ፤ " አንዳንድ የሠልፉ ተሰታፊዎች በተቋማት ላይ #ድንጋይ በመወርወር እና ገበያ በመበተን ሁከት ለመፍጠር ሞክረዋል " ብለዋል።

" የፀጥታ አባላት የጉዳቱ መጠን ሳይሰፋ ለመቆጣጠር ችለዋል " ሲሉም ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።

Credit : #ዶቼቨለ_ሬድዮ
Photo : Social Media

@tikvahethiopia