TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ደሴ

ከደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተዘርፈው ሊወጡ የነበሩ የህክምና ቁሳቁሶች ተያዙ።

ትላንት ነሀሴ 2 በግምት ከሌሊቱ 6 ሰአት ከደሴ ከተማ አጠቃላይ ስፔሻለይዝድ ሆስፒታል ከ638 ሺህ ብር በላይ የሚገመቱ የህክምና ማሽን ተሠርቀው ሊወጡ ሲሉ እጅ ከፍንጅ መያዛቸው ተገለፀ።

ተሰርቆ ሊወጣ የነበረው ፦

- የላብራቶሪ ማሽን 4 ኦሎምፐስ (olomps) ማይክሮስኮፕ፣
- 1 ላቦመድ (labomed) ማይክሮስኮፕ፣
- 1 የኬሚስትሪ ማሽን(ዲያሚንሽን ማሽን ትንሿ ፕሪንተር፣
- 1 NEO-BIL የቢል ማሽን፣
- 5 አዲስ ዶግለር የበር ቁልፍና የተለያዩ የኤሌትሪክ ገመድና ቁሳቁስ ነው።

የህክምና ቁሳቁሶቹ ሰርቀው ሊወጡ ሲሉ እጅ ከፍንጅ በጥበቃ ሰራተኞች የተያዙ ግለሰቦች መኖራቸው የተገለፀ ሲሆን በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው ነው።

ድርጊቱን የፈፀሙ ግለሰቦችን በተመለከተ ዝርዝር መረጃ አልተገለፀም።

የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሃይማኖት አየለ ፤ ከአሁን በፊትም #በሆስፒታሉ_ሰራተኞች ከ6 መቶ ሺ ብር በላይ የሚገመቱ ለክሮኒክ በሽታ የሚታዘዙ መድሀኒትና ሌሎች መድሀኒቶች መዘረፉን ተነግረዋል።

ዘረፋ ያካሄዱ 3 ሰራተኞች ከስራ ተባረው በህግ እንዲጠየቁ ሲደረገ አንድ ባለሙያ ላይ ከደረጀ ዝቅ እንዲል መደረጉን ገልፀዋል።

ዶ/ር ሃይማኖት ፤ " የጥበቃ ስራውን አጠናክረን ስንቀሳቀስ የስርቆት ወንጀሉ ከውጭና ከውስጥ የተያያዘ ቁርኝት ያላቸው የሌብነት ሰንሰለት እንዳለ ተረድተናልና ህብረተሠቡ ሊያግዘንና ሊተባበረን ይገባል " ብለዋል።

መረጃውን ከደሴ ኮሚኒኬሽን ነው ያገኘነው።

@tikvahethiopia