TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
መቐለ ዩኒቨርሲቲ👆

የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት በግቢው ውስጥ ደም እየለገሱ ይገኛሉ!! #መቐለ_ዩኒቨርሲቲ #Mekelle_University

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የአንድ እናት ልጆች ነን መስመር አይለየን...
የአንድ ቤት ልጆች ነን መስመር አይለየን...

#መቐለ_ዩኒቨርሲቲ የሰላም አምባሳደር!
#ፍቅር #ተስፋ #አንድነት #መቐለ_ዩኒቨርሲቲ
ኦቦ #በቀለ_ገርባ ~~ #መቐለ_ዩኒቨርሲቲ

የፌደራል ሥርዓት አወቃቀር #ለቋንቋዎች እድገት መሠረት ከመጣሉ ባለፈ ኅብረተሰቡም ባደገበት ቋንቋ የመንግሥት አገልግሎት ለማግኘት እንደሚያስችለው የቋንቋ ምሁሩና ፖለቲከኛው አቶ #በቀለ_ገርባ ገለጹ። "የኢዮጵያ ቋንቋዎችና ጠቀሜታዎች" በሚል የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ያዘጋጀው መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።

ተጨማሪ የንብቡ👇
https://telegra.ph/Mekelle-07-25
የTIKVAH-ETH #የStopHateSpeech ሀገር አቀፍ ዘመቻዎች/በዩኒቨርሲቲ ደረጃ/ና በየተለያዩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ውስጥ የተደረጉ ጉብኝቶችን ለመከታተል #የዩትዩብ ቻናላችንን ይጎብኙ!

#ሀረማያ #ጅማ #ወልቂጤ #ሀዋሳ #ወላይታ_ሶዶ #አርባምንጭ #መቐለ #ዋቻሞ #ወሎ #ደብረብርሃን #ወልዲያ

Watch ""የአንድ እናት ልጆች ነን" በመቐለ ዩኒቨርሲቲ #TIKVAH_ETHIOPIA" on YouTube
https://youtu.be/qjyt56okb3U
#መቐለ_ዩኒቨርሲቲ

በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን የሚከታተሉ እና በዘንድሮው ዓመት ለምረቃ የሚበቁ ተማሪዎች ምንም አይነት ችግር ሳይገጥማቸው መቆየታቸውን ተናግረው ሆኖም ግን ለከፍተኛ ርሃብ እና የውሃ ጥም ተዳርገው መቆየታቸውንና በአሁኑ ሰዓት የመከላከያ ሰራዊቱ ድጋፍ እያደረገላቸው ይገኛል።

በአሁን ሰዓት ተማሪዎቹ ምንም አይነት ምግብ የሚያዘጋጁ ሰራተኞች በቅጥር ግቢው ባለመኖራቸው ምክንያት እየተቸገሩ መሆናቸውን በመግለፅ መንግስት እና የሚመለከታቸው አካላት በጉዳዩ ላይ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጣቸውም በአፅንኦት ጠይቀዋል።

መረጃውን የላከልን በራያ ግንባር የሚገኘው ሃምሳ አለቃ አበበ ሰማኝ ነው።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#መቐለ_ዩኒቨርሲቲ

ሀምሳ ሁለት (52) ተማሪዎችና አንድ መምህር ከመቐለ ዩኒቨርሲቲ ኩሓ ካምፓስ በመውጣት በመኪና ወደ አባላ ከተማ (አፋር) መጓዛቸውንና ከዚያም ከአባላ ወደ አፍዴራ ሲጓዙ 'ስልሳ ስድስት' የሚባል የፍተሻ ጣቢያ ላይ ላይ በአፋር ክልል ፖሊስ አግኝቶ ተማሪ መሆናቸው ካረጋገጠ በኋላ ዛሬ ከሰዐት ለሠመራ ዩኒቨርሲቲ ማስረከቡን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ሰምቷል።

በመጀመሪያ 19 ተማሪዎች እና አንድ መምህር በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ድጋፍ ዛሬ ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸው የተነገረ ሲሆን ቀሪ 33ቱን የሠመራ ዩኒቨርሲቲ ነገ ጠዋት ተማሪዎቹን በባስ አሽኛኝት እንደሚያደረግላቸው የህዝብ ግንኙነት ባለሙያው ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አረጋግጠዋል።

ተማሪዎቹ በጉዟቸው ወቅይ ምንም የተለየ ችግር ባይገጥማቸውም ፤ ምግብ ባለማግኘታቸው አስከፊ ግዜ እንዳሳለፉ አልደበቁም። ከ52ቱ ተማሪዎች አንድ ሴት ተማሪ ያለች ሲሆኑ አብዛኛዎች የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ናቸው።

በተማሪዎቹ ጉዳይ አስተያየት የጠየቅነው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር "አዲስ ነገር ሲኖር ጠቅለል አርገን" እናሳውቃለን ብሏል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መረጃዎች በ @tikvahuniversity በስፋት ማግኘት ይቻላል።

https://publielectoral.lat/joinchat/RYD_4tbNBwRoKR2h

@tikvahethiopia
#መቐለ_ዩኒቨርሲቲ

" ተማሪዎቻችንን እንደገና ለመቀበል ዝግጁ ስንሆን ይፋዊ መግለጫ እንሰጣለን " - ዶ/ር ፋና ሀጎስ (የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት)

ከትላንት ምሽት አንስቶ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች መቐለ ዩኒቨርሲቲን የሚመለከቱ መረጃዎች እየተሰራጩ ይገኛሉ።

እነዚህ መረጃዎች ፦
- ዩኒቨርሲቲው ወደ መማር ማስተማር ስራው እዲመለስ መወሰኑ፣
- በጦርነቱ አቋርጦ የነበረውን ስራ ከመጪው ሳምንት አንስቶ እንደሚጀምር፣
- በመንግስት በኩል አስፈላጊው #በጀት እንደተለቀቀለት፣
- 24 ሺህ ነባር ተማሪዎችን በቀጣይ 4 ወር ትምህርት እንዲያጠናቅቁ እንደሚያደርግ
- ከመስከረም 2016 ጀምሮ አዲስ ተማሪዎችን እንደሚቀበል የሚገልፁ ናቸው።

ነገር ግን ይህ የተሳሳተ መረጃ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ገልጸዋል።

መቐለ ዩኒቨርሲቲም ቢሆን በይፋዊ የፌስቡክ እና የትዊተር አካውንቱ ላይ ምንም አይነት መረጃ አልለጠፈም።

የተሰራጨውን መረጃ በተመለከተ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋና ሀጎስ ለ" ኢትዮጵያ ቼክ " መረጃ ማጣሪያ ድረገፅ በሰጡት ቃል ፥ ዩኒቨርሲቲው ስራ ለመጀመር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቅርበት እየሰራ ቢሆንም በዩኒቨርሲቲው ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመጠገን የራሱን ጊዜና ሂደት እንደሚወስድ ተናግረዋል።

ዶ/ር ፋና " ዩኒቨርሲቲው ሥራውን ይጀምራል ነገር ግን በሚቀጥለው ሳምንት አይደለም ፤ በእርግጥ ይህን ለማድረግ ወራትን ይወስዳል " ሲሉ ተናግረዋል።

ዶ/ር ፋና እስካሁን መቐለ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች ጥሪ እንዳላደረገ ገልፀው " እኛ (ዩኒቨርሲቲው ወይም የትምህርት ሚኒስቴር) ተማሪዎቻችንን እንደገና ለመቀበል ዝግጁ ስንሆን ይፋዊ መግለጫ እንሰጣለን " ሲሉ አሳውቀዋል።

Credit : ethiopiacheck.org

@tikvahethiopia
" #ኢትዮጵያን በማስጠራቴ ትልቅ ክብር ይሰማኛል " - የወጣቱ የህዋ ሳይንስ ተመራማሪ ትንሳኤ አለማየሁ

#ኢትዮጵያዊው የሕዋ ሳይንስ ተመራማሪ ወጣት ትንሳኤ አለማየሁ ዓለም አቀፉ የአስትሮኖቲካል ፌደሬሽን የ2023 ወጣት የህዋ መሪዎች ብሎ ከሰየማቸው አምስት ተመራማሪዎች አንዱ ሆኗል።

ፌደሬሽኑ ስያሜውን እውቀታቸውንና ልምዳቸውን ለሌሎች ወጣቶች በማጋራትና ማህበረሰብ በመድረስ እንዲሁም በትምህርት እና ምርምር ለአስትሮኖቲክ መስክ አበርክቶ ላደረጉ ወጣቶች የሚሰጠው ዕውቅና ነው።

ፌደሬሽኑ ሽልማቱን በባኩ አዘርባጃን በመስከረም 2016 ዓ.ም በሚደረገው በ74ኛው የዓለም አቀፉ የአስትሮኖቲካል ኮንግረስ ለወጣት ተመራማሪዎቹ እንደሚሰጥ ተገልጿል።

በዓለም አቀፉ ፌደሬሽን በወጣቶች ዘርፍ የሚሰጠውን ትልቁን ሽልማት በማግኘቱ ከፍተኛ ደስታ እንደሚሰማው ትንሳኤ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግሯል።

ሽልማቱን በማግኘት ኢትዮጵያን በማስጠራቱ ትልቅ ክብር እንደሚሰማውም ገልጿል።

በሜካኒካል ምህንድስና የመጀመሪያ ዲግሪውን ከ #መቐለ_ዩኒቨርሲቲ ያገኘው ትንሳኤ አለማየሁ ፤ ለህዋ ሳይንስ ባለው ራዕይ እና ለዘርፉ ላደረገው አበርክቶ በርካታ ሽልማቶችን አጊኝቷል። 

ካገኛቸው ሽልማቶች ውስጥ ፦

- እ.ኤ.አ. በ2022 ከዓለም አቀፉ የጠፈር ተመራማሪዎች ፌደሬሽን (አይኤኤፍ) የተበረከተውን ተስፋ የተጣለባቸው ስፔስ መሪዎች ሽልማትን፤

- ከ30 አመት በታች የአፍሪካ ስፔስ ኢንዱስትሪ ሽልማት፤

- በ2021 ከስፔስ ኢን አፍሪካ እና ከSGAC የግሎባል ግራንት ፕሮግራም ሽልማትን፤

- በ2019 ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ የወጣት ሕዋ አምባሳደርን ጨምሮ ሌሎች ብዙ ሽልማቶችን እና እውቅናዎችን አግኝቷል።

ወጣቱ ተመራማሪ አሁን ላይ የዓለም ዐቀፉ የህዋ ጄነሬሽን አማካሪ ም/ቤት (SGAC) የአፍሪካ ቀጣናዊ አስተባባሪ በመሆን እያገለገለ ይገኛል።

https://www.iafastro.org/news/the-iaf-is-proud-to-introduce-the-2023-iaf-young-space-leaders.html

More : @tikvahuniversity