TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከዓለም ዙሪያ ፦

➡️ #አሜሪካ - በኒውዮርክ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሂዷል። ሰልፉ በመሳሪያ የገዙ ጥቃቶችን ለማውገዝ የተካሄደ ነው። ሰልፉ የተካሄደው አንድ ወጣት በቴክሳስ ሮብ በሚሰኝ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 19 ህፃናት ተማሪዎችን እና 2 መምህራንን በአሰቃቂ ሁኔታ ከገደለ ከቀናት በኃላ ነው።

➡️ #ስፔን - በሰሜናዊ ስፔን ላ ሪዮጃ ክልል በባዮዲዝል ማምረቻ ፋብሪካ ላይ በደረሰ ፍንዳታ ቢያንስ 2 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል።

➡️ #የመን - በየመን አደን ከተማ ሰዎች በሚበዙበት በተጨናነቀ ገበያ ላይ በደረሰ ፍንዳታ በትንሹ 4 ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች መቁሰላቸው ታውቋል፤ እስካሁን ለጥቃቱ ኃላፊነት ወስዳለሁ ብሎ ብቅ ያለ የለም።

➡️ #ሱዳን - ከወራት በፊት በሱዳን የተካሄደውም ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ተከትሎ የተነሳው ተቃውሞ አሁንም ያልበረደ ሲሆን ትላንትና በሺዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚዎች በካርቱም ጎዳናዎች ላይ ተቃውሞ አሰምተዋል። የጥቅምቱ መፈንቅለ መንግስት ሀገሪቱን ወደ ፖለቲካዊ ቀውስ አስገብቷል።

➡️ #ጣልያን - የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ማሪዮ ድራጊ የሩሲያው ፕሬዜዳንህ ፑቲን አሁን ላይ በዓለም የሚየው የምግብ ችግር "በሩሲያ ላይ የተጣለው ማዕቀብ ነው " ብለው እንደነገራቸው ተናግረዋል። የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ከጀመረ አንስቶ ምዕራባውያን ሀገራት ሩስያ ላይ እጅግ ከፍተኛ የሚባሉ ማዕቀቦችን እየጣሉ እንደሆነ ይታወቃል። ለእነዚህ ማዕቀቦችም ሩስያ ምላሽ ከመስጠት ወደኃላ አላለችም።

➡️ #ቱርክ #ፈረንሳይ - የቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ከፈረንሳይ ፕሬዜዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የስውዲን እና ፊንላንድ ለNATO አባልነት ባቀረቡት ማመልከቻ፣ በዩክሬን ሩስያ ጦርነት፣ በቀጠናዊ ጉዳዮች እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ተገናኝተው መክረዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#ጣልያን

በስደተኞች ቁጥር መጨመር እየተቸገረ ያለው የጣሊያን መንግስት ትናላንት ወደ ሀገሪቱ የሚገቡ ስደተኞች የሚታሰሩበት ጊዜ እንዲረዝም እና ህጋዊ የመኖሪያ ፍቃድ የሌላቸው ተይዘው እንዲመለሱ የሚያደርግ ህግ አጽድቋል።

ይህ እርምጃ የተወሰደው ባለፈው ሳምንት 10ሺ የሚሆኑ ስደኞች በጣሊያኗ ላምፔዱሳ ወደብ መድረሳቸውን ተከትሎ ነው።

የስደተኞቹ ወደ ጣሊያን መጉረፍ ህገወጥ ስደተኞችን ለመቆጣጠር ቃል ለገቡት የቀኝ ዘመም ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ትልቅ ችግር እንደፈጠረባቸው ተነግሯል።

ሜሎኒ ፤ በካቢኔ ስብሰብ መጀመሪያ ላይ  እንደገለጹት ወደ ሀገራቸው ለመመስ የሚጠባቀቁ ስደተኞች  ከ6 እስከ 18 ወራት እስራት ይጠብቃቸዋል።

የመንግስት ምንጮች ካቢኔው መንግስት ያቀረበውን ህግ ማጽደቁን እና ራቅ ባሉ ቦታቸው እስርቤቶች እንደሚሰሩ መወሰኑን ገልጸዋል።

ሜሎኒ ቀደም ሲል በነበሩት የስደተኞች ፖሊሲዎች ምክንያት የተዳከሙትን የማቆያ ቦታዎች ወይም እስርቤቶችን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል።

ህገወጥ ስደተኞች በአስቸኳይ ወደ ሀገራቸው የማይላኩ ከሆነ የሚቆዩበት እስርቤት ይኖራል ያሉት ሜሎኒ ስደተኞችን ለማቆም ከዚህ በፊት የተደረጉ ሙከራዎች ሳይሳኩ መቅረታቸውን ገልጸዋል።

የጣሊያን ባለስልጣናት አብዛኞቹ ስደተኞች በኢኮኖሚ ምክንያት የሚሰደዱ ስለሆነ ጥገኝነት ለመጠየቅ መስፈርት አያሟሉም ይላሉ።

ሜሎኒ በካቢኔ ስብሰብ መጀመሪያ ላይ  እንደገለጹት ወደ ሀገራቸው ለመመስ የሚጠባቀቁ ስደተኞች  ከ6 እስከ 18 ወራት እስራት ይጠብቃቸዋል።

መረጃው የአል ዓይን ኒውስ ነው።

@tikvahethiopia