TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የኢቦላ ወረርሽኝ‼️

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በቅርቡ ያገረሸው ኢቦላ ወረርሽኝ በአገሪቷ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና #አሰከፊ ነው ሲል የአገሪቷ ጤና ጥበቃ ሚንስትር አስታውቀዋል።

ከባለፉት አራት ወራት ጀምሮ ቢያንስ 200 ሰዎች በወረርሽኙ ሕይወታቸው ሲያልፍ ወደ 300 የሚሆኑ የተጠረጠሩ ህመምተኞች ተገኝተዋል።

ወረርሽኙን ለመግታት የተለያዩ ጥረቶች እየተደረገ ሲሆን እስካሁን 25 ሺህ ለሚሆኑ ሰዎች #ክትባት ተሰጥቷል።

ይሁን እንጂ የአገሪቱ ፖለቲካዊ #አለመረጋጋትና የጤና ባለሙያዎች ላይ በተለያየ ጊዜ ጥቃት በመድረሱ ለዓመታት ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት ተፈታትኖታል።

የጤና ጥበቃው ሚንስትር ኦሊ ኢሉንጋ በዚህ ሰዓት 319 በበሽታው የተያዙና 198 ሞት መመዝገቡን ገልፀዋል።

"ቤተሰቦቻቸውን ላጡ፣ ያለ አሳዳጊ ለቀሩ ሕፃናትና ለተበተኑ የቤተሰብ አባላት የተሰማኝን ሀዘን እገልፃለሁ ፤ መፅናናትን እመኛለሁ፤ በፀሎትም አስባቸዋለሁ" ሲሉ ተናግረዋል።

ባለስልጣኑ እንደተናገሩት ግማሽ ያህሉ ተጎጂዎች 800 ሺህ ህዝብ ከሚኖርባት የሰሜናዊ ኪቩ ግዛት ቤኒ ነዋሪዎች ናቸው።

አገሪቱ በአውሮፓውያኑ 1976 ካጋጠማት ስሙ በውል ካልታወቀው ወረርሽኝ በኋላ የአሁኑ በጣም አሰቃቂውና አስፈሪው ነው።

ኢቦላ ከሰውነት ከሚወጣ ፈሻሽ እና ሌሎች ኢንፌክሽኖች አማካኝነት ይተላለፋል፤ ምልክቱም ጉንፋን መሳይ ህመም፣ ማስታወክ፣ ተቅማጥ፣ ውስጣዊና ውጫዊ መድማት ናቸው።

ምንጭ፦ OBN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኮሮና ክትባት በአመት ውስጥ እውን ሊሆን ይችላል!

በአውሮፓ ለሚዘጋጁ ክትባቶች ፍቃድ የሚሰጠው የአውሮፓ ህብረት ኤጀንሲ ተስፋ የተጣለበት የኮሮና ቫይረስ #ክትባት በቀጣዩ አንድ (1) ዓመት ውስጥ እውን ሊሆን እንደሚችል አስታውቋል - #AlAin

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#Philippines

"ክትባት እስካልተገኘ ድረስ ትምህርት ቤቶች አይከፈቱም!" -ፕሬዘዳንት ሮድሪጎ ዱቴርቴ

የፊሊፒንስ ፕሬዘዳንት የሆኑት ሮድሪጎ ዱቴርቴ በኮቪድ-19 ምክንያት የተቋረጠው ትምህርት ዘላቂ እና አስተማማኝ መፍትሄ እስካልተገኘለት ድረስ እንደማይጀመረ አሳውቀዋል።

ፕሬዘዳንቱ ሰኞ ዕለት በተሰራጨ የቴሌቪዥን መልዕክታቸው #ክትባት እስካልተገኘ ድረስ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት እንደማይልኩ ገልፀዋል።

አክለውም የተማሪዎች ደህንነት ባልተጠበቀበትና ለዚህ ወረርሽኝ ክትባት ባልተገኘበት ሁኔታ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት መላክ ችግሩ ይባብሰዋል ሲሉ ተናግረዋል።

በፊሊፒንስ እስካሁን ድረስ ባለው መረጃ 15,588 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከነዚህ መኃል 921 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 3,598 ሰዎች በተደረገላቸው ህክምና አገግመዋል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot