TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሠላም ለራስ ነው!

ሶሪያ፣ሊቢያ፣የመን...በእነዚህ ሃገራት ሰዎች እንደዋዛ ህይወታቸውን ያጣሉ፤ በአሁን ቅጽበትና ባሉበት ስፍራ መኖራቸውን እንጂ የሚቀጥለው ትንፋሻቸው ይኑር አይኖር ማረጋጋጥ አይችሉም። በማንኛውም ስፍራና ጊዜ #ሞት አለ። ሰርቶ መሰረታዊ ፍላጎቶችን ማሟላት አይቻልም፤ ስራ የለም። ሃብት ማፍራት የሚባለው ነገር የማይጨበጥ ቅዠት ነው። እነዚህ ሃገራት #የተተረማመሱት ለፖለቲካዊ ነጻነቶች በተደረጉ እንቅስቃሴዎች ነው ቢባልም አሁን ግን ፖለቲካዊ መብትና ነጻነት የሚባሉት ነገሮች ትርጉም አጥተዋል። አመለካከትን ማራመድ፣ መደራጀት፣ ሃሳብን መግለጽ፣ ምርጫ፣ የስልጣን ውክልና፣ መንግስት፣ የህግ የበላይነት የሚባሉት ነገሮች ማረፊያ መሬት አጥተዋል፤ ማረፊያቸው ሰላም ነበርና።

ሰላም ለሰዎች ተለጣፊ ነገር ሳይሆን መሰረታዊና የህልውና ጉዳይ ነው!

የፅሁፉ ባለቤት ኢብሳ ነመራ--TIKVAH-ETH ለዛሬው ቀን እንዲሆን መርጦ የወሰደው!
@tsegabwolde @tikvahethiopia