የኳታር መንግስት ተጨማሪ ውሳኔዎች፦
- በጣም አስፈላጊ ለሆኑ ጉዳዮች ካልሆነ በቀር በትንንሽ መኪና ፣ በአውቶቡስ እና በጭነት መኪና ከሚደረግ ጉዞ በስተቀር በአንድ መኪና ውስጥ ከአንድ በላይ ሰው መግባት የለበትም፤ በመኪና ውስጥ መሰባሰብ ክልክል ነው።
- በየትኛውም ቦታ (ኮርኒሽን ጨምሮ) ምንም ዓይነት መሰባሰብ ሊኖር አይገባም። ለዚህም በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች በተንቀሳቃሽ የፖሊስ መኪኖች (mobile patrols) አማካኝነት ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግ ሲሆን፣ ይህን ተግባራዊ የማያደርጉ ሰዎች በቁጥጥር ስር ይውላሉ።
- መንግስት በምግብ አቅራቢ ድርጅቶች (Food delivery companies) ጥብቅ ቁጥጥር ያደርጋል፤ የንጽህና መስፈርቶችን በትክክል ያሟሉ መሆኑ ይጠበቅባቸዋል።
- በርካታ ሰዎች ሊሰባሰቡባቸው የሚችሉ የምግብ አቅራቢ ድርጅቶች ሊዘጉ ይችላሉ።
- ሁሉም የመዝናኛ ፓርኮች (parks) እና የባህር ዳር የሕዝብ መዝናኛዎች (public beaches) ላልተወሰነ ጊዜ ዝግ ይሆናሉ።
- እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ብዛት 481 የደረሰ ሲሆን፣ 27 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
#EthiopianEmbassyDoha
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
- በጣም አስፈላጊ ለሆኑ ጉዳዮች ካልሆነ በቀር በትንንሽ መኪና ፣ በአውቶቡስ እና በጭነት መኪና ከሚደረግ ጉዞ በስተቀር በአንድ መኪና ውስጥ ከአንድ በላይ ሰው መግባት የለበትም፤ በመኪና ውስጥ መሰባሰብ ክልክል ነው።
- በየትኛውም ቦታ (ኮርኒሽን ጨምሮ) ምንም ዓይነት መሰባሰብ ሊኖር አይገባም። ለዚህም በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች በተንቀሳቃሽ የፖሊስ መኪኖች (mobile patrols) አማካኝነት ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግ ሲሆን፣ ይህን ተግባራዊ የማያደርጉ ሰዎች በቁጥጥር ስር ይውላሉ።
- መንግስት በምግብ አቅራቢ ድርጅቶች (Food delivery companies) ጥብቅ ቁጥጥር ያደርጋል፤ የንጽህና መስፈርቶችን በትክክል ያሟሉ መሆኑ ይጠበቅባቸዋል።
- በርካታ ሰዎች ሊሰባሰቡባቸው የሚችሉ የምግብ አቅራቢ ድርጅቶች ሊዘጉ ይችላሉ።
- ሁሉም የመዝናኛ ፓርኮች (parks) እና የባህር ዳር የሕዝብ መዝናኛዎች (public beaches) ላልተወሰነ ጊዜ ዝግ ይሆናሉ።
- እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ብዛት 481 የደረሰ ሲሆን፣ 27 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
#EthiopianEmbassyDoha
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኳታር ተጥለው የቆዩ እገዳዎች እየተነሱ ነው!
በኳታር መንግስት የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመግታት ተጥሎ የቆዩ እገዳዎች ቀስ በቀስ እየተነሱ ነው። በዛሬው እለት የመጀመሪያ ደረጃ (First Phase) ውሳኔዎች ተግባራዊ መሆን ጀምረዋል።
በዚህም መሰረት፦
- ከጁምዓ ጸሎት በስተቀር በሌሎቹ ቀናት መስጊዶች በከፊል ክፍት መሆን ጀምረዋል።
- 20 ከመቶ የሚሆኑ የተለያዩ ተቋማት ሰራተኞች ወደ ስራ ገበታቸው ይመለሳሉ።
- ትልልቅ የገበያ አዳራሾች (Malls) እና ማዕከላት በከፊል (እስከ 30% አቅም) ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 2፡00 ሰዓት (8:00 AM to 8:00 PM) ክፍት ይሆናሉ። ሆኖም እነዚህ ማዕከላት ቅዳሜ እና አርብ ዝግ ይሆናሉ።
- የግል የህክምና ማዕከላት (እስከ 40% አቅም ያላቸው) ክፍት ይሆናሉ።
- 8 የመዝናኛ ፓርኮች ጠዋት ከንጋቱ 10፡00 ሰዓት እስከ 3፡00 ሰዓት (4፡00 AM – 9:00 AM) እና ከሰዓት በኋላ ከ 10፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 4፡00 ሰዓት (4:00 PM – 10:00 PM) ለስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ክፍት ይሆናሉ።
#EthiopianEmbassyDoha
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኳታር መንግስት የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመግታት ተጥሎ የቆዩ እገዳዎች ቀስ በቀስ እየተነሱ ነው። በዛሬው እለት የመጀመሪያ ደረጃ (First Phase) ውሳኔዎች ተግባራዊ መሆን ጀምረዋል።
በዚህም መሰረት፦
- ከጁምዓ ጸሎት በስተቀር በሌሎቹ ቀናት መስጊዶች በከፊል ክፍት መሆን ጀምረዋል።
- 20 ከመቶ የሚሆኑ የተለያዩ ተቋማት ሰራተኞች ወደ ስራ ገበታቸው ይመለሳሉ።
- ትልልቅ የገበያ አዳራሾች (Malls) እና ማዕከላት በከፊል (እስከ 30% አቅም) ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 2፡00 ሰዓት (8:00 AM to 8:00 PM) ክፍት ይሆናሉ። ሆኖም እነዚህ ማዕከላት ቅዳሜ እና አርብ ዝግ ይሆናሉ።
- የግል የህክምና ማዕከላት (እስከ 40% አቅም ያላቸው) ክፍት ይሆናሉ።
- 8 የመዝናኛ ፓርኮች ጠዋት ከንጋቱ 10፡00 ሰዓት እስከ 3፡00 ሰዓት (4፡00 AM – 9:00 AM) እና ከሰዓት በኋላ ከ 10፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 4፡00 ሰዓት (4:00 PM – 10:00 PM) ለስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ክፍት ይሆናሉ።
#EthiopianEmbassyDoha
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia