TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የኳታር መንግስት ተጨማሪ ውሳኔዎች፦

- በጣም አስፈላጊ ለሆኑ ጉዳዮች ካልሆነ በቀር በትንንሽ መኪና ፣ በአውቶቡስ እና በጭነት መኪና ከሚደረግ ጉዞ በስተቀር በአንድ መኪና ውስጥ ከአንድ በላይ ሰው መግባት የለበትም፤ በመኪና ውስጥ መሰባሰብ ክልክል ነው።

- በየትኛውም ቦታ (ኮርኒሽን ጨምሮ) ምንም ዓይነት መሰባሰብ ሊኖር አይገባም። ለዚህም በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች በተንቀሳቃሽ የፖሊስ መኪኖች (mobile patrols) አማካኝነት ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግ ሲሆን፣ ይህን ተግባራዊ የማያደርጉ ሰዎች በቁጥጥር ስር ይውላሉ።

- መንግስት በምግብ አቅራቢ ድርጅቶች (Food delivery companies) ጥብቅ ቁጥጥር ያደርጋል፤ የንጽህና መስፈርቶችን በትክክል ያሟሉ መሆኑ ይጠበቅባቸዋል።

- በርካታ ሰዎች ሊሰባሰቡባቸው የሚችሉ የምግብ አቅራቢ ድርጅቶች ሊዘጉ ይችላሉ።

- ሁሉም የመዝናኛ ፓርኮች (parks) እና የባህር ዳር የሕዝብ መዝናኛዎች (public beaches) ላልተወሰነ ጊዜ ዝግ ይሆናሉ።

- እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ብዛት 481 የደረሰ ሲሆን፣ 27 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።

#EthiopianEmbassyDoha
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኳታር ተጥለው የቆዩ እገዳዎች እየተነሱ ነው!

በኳታር መንግስት የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመግታት ተጥሎ የቆዩ እገዳዎች ቀስ በቀስ እየተነሱ ነው። በዛሬው እለት የመጀመሪያ ደረጃ (First Phase) ውሳኔዎች ተግባራዊ መሆን ጀምረዋል።

በዚህም መሰረት፦

- ከጁምዓ ጸሎት በስተቀር በሌሎቹ ቀናት መስጊዶች በከፊል ክፍት መሆን ጀምረዋል።

- 20 ከመቶ የሚሆኑ የተለያዩ ተቋማት ሰራተኞች ወደ ስራ ገበታቸው ይመለሳሉ።

- ትልልቅ የገበያ አዳራሾች (Malls) እና ማዕከላት በከፊል (እስከ 30% አቅም) ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 2፡00 ሰዓት (8:00 AM to 8:00 PM) ክፍት ይሆናሉ። ሆኖም እነዚህ ማዕከላት ቅዳሜ እና አርብ ዝግ ይሆናሉ።

- የግል የህክምና ማዕከላት (እስከ 40% አቅም ያላቸው) ክፍት ይሆናሉ።

- 8 የመዝናኛ ፓርኮች ጠዋት ከንጋቱ 10፡00 ሰዓት እስከ 3፡00 ሰዓት (4፡00 AM – 9:00 AM) እና ከሰዓት በኋላ ከ 10፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 4፡00 ሰዓት (4:00 PM – 10:00 PM) ለስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ክፍት ይሆናሉ።

#EthiopianEmbassyDoha
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia