TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከአዲስ አበባ...

"ትላንት ሰሚት ኮንዶሚንየም #ሙስሊም#ክርስቲያኑ ወጥቶ ለሁሉም የሚሆን ማዕድ ቀርቦ ደስ በሚል ሁኔታ በመተሳሰብ ፤ በመዋደድ ጥሩ ጊዜ አሳልፈናል።" H

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ረመዷን

በመላው ዓለም ላይ የሚታወቁት የዝምባብዌ ዜግነት ያላቸው የእስልምና መሁር ሙፍቲ  ኢስማኤል ሜንክ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ስለ ቅዱሱ የረመዷን ወር እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል ፦

ሙፍቲ  ኢስማኤል ሜንክ (ዶ/ር) ፦

" ረመዷን ምንድን ነው ? ሰዎች እየፆምን ነው ይላሉ ይህ ግን የረመዷን አንዱ ክፍል ብቻ ነው።

ረመዷን ፦
🤲 #የሰላም ወር ነው፤
🤲 #የመረጋጋት ወር ነው፤
🤲 #የመፈወሻ ወር ነው፤
🤲 #የቸርነት ወር ነው፤
🤲 #የምህረት ወር ነው፤
🤲 #የይቅርታ ወር ነው፤
🤲 #ጀነትን የምናገኝበት ወር ነው፤
🤲 ይህ ወር #ሙስሊም መሆናችንን የምናከብረበት ነው ፤ ሙስሊም በመሆናችን #ራስን_መግዛትን የምንለማመድበት የፈለግነውን ብቻ ሳይሆን ሁሉን ቻይ የሆነው አላህ የወሰነውን የምናደርግበት ወር ነው ፤  ሱብሃንአላህ ! ስለዚህ ለአላህ ቃል ጥረት ማድረግ ግዴታችን ነው። "

መልካም #የረመዷን_ጾም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንዲሆን እንመኛለን።

#TikvahFamily

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

በደበሶ ከተማ በመኪና አደጋ የሞቱ ምእመናን ዛሬ ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል።

በምዕራብ ሐረርጌ ደበሶ ከተማ ትላንት ጥር 12/05/2016 ዓ/ም የቃና ዘገሊላ ክብረ በዓል ዕለት ታቦታትን አጅበው በመጓዝ ላይ የነበሩ ምእመናን ላይ ከድሬደዋ የሚመጣ ከባድ የጭነት መኪና ባደረሰው አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ሰብከት ማሳወቁ ይታወሳል።

ሕይወታቸው ያለፈው ምእመናን ዛሬ ልባቸው በሀዘን የተሰበረ እጅግ በርካታ ምእመናን በተገኙበት ከቀኑ በ7:45 ላይ ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል።

ሀገረ ስብከቱ ፤ " ከተቀበሩት መካከል ሦስቱ ጨቅላ ህጻናት ሲሆኑ አንዱ ሕይወቱ ያለፈው ግለሰብ የቀበሌው ሚኒሻ ሃይማኖቱ #ሙስሊም ስለሆነ በወገኖቻችን በሙስሊሞች የቀብር ስፍራ ተቀብሯል። " ሲል አሳውቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ሰብከት ማግኘቱን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ረመዷን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዜዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ፦ " ታላቁ የረመዳን ወር የእዝነት፣ የመተሳሰብ፣ የምህረት ወር በመኾኑ ደካሞችን፣ ችግረኞችን፣ ተፈናቃዮችን እንዲሁም ወላጅ አልባ ሕጻናትን በመርዳትና ማዕዳችንን በማካፈል በመተሳሰብና አላህን በመለመን ልናሳልፈው ይገባል። የረመዳን ወር የእዝነት፣ የምህረትና ከእሳት ነጃ የምንወጣበት፣ አላህ ዘንድ ተቀባይነት…
#ረመዷን

ሙፍቲ ኢስማኤል ሜንክ (ዶ/ር) ፦

" ረመዷን ምንድን ነው ? ሰዎች እየፆምን ነው ይላሉ ይህ ግን የረመዷን አንዱ ክፍል ብቻ ነው።

ረመዷን ፦
🤲 #የሰላም ወር ነው፤
🤲 #የመረጋጋት ወር ነው፤
🤲 #የመፈወሻ ወር ነው፤
🤲 #የቸርነት ወር ነው፤
🤲 #የምህረት ወር ነው፤
🤲 #የይቅርታ ወር ነው፤
🤲 #ጀነትን የምናገኝበት ወር ነው፤
🤲 ይህ ወር #ሙስሊም መሆናችንን የምናከብረበት ነው ፤ ሙስሊም በመሆናችን #ራስን_መግዛትን የምንለማመድበት የፈለግነውን ብቻ ሳይሆን ሁሉን ቻይ የሆነው አላህ የወሰነውን የምናደርግበት ወር ነው ፤  ሱብሃንአላህ ! ስለዚህ ለአላህ ቃል ጥረት ማድረግ ግዴታችን ነው። "

መልካም #የረመዷን_ጾም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንዲሆን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይመኛል።

@tikvahethiopia