TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AtoAknawKawza

ከደቡብ ክልል ጤና ቢሮ የተሰጠ መረጃ፦

በደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ/ መንግስት ከከምባታ ጠምባሮና ሐድያ ዞኖች በላፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በደቡብ ህብረተሰብ ጤና ላብራቶሪ በተደረገው 59 የላብራቶሪ ምርመራ ነው 2 (ሁለት) ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው።

የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ ፦

ታማሚ 1 - 22 ዓመት ወጣት ፤ ከሻሾጎ ወረዳ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያለው ፤ በ23/08/2012 ከኬንያ በሞያሌ በኩል ከተመለሰው ታማሚ ጋር ንክኪ #ያለውና አሁን በሆሳዕና ከተማ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ።

ታማሚ 2 - የ21 ዓመት ወጣት ፤ ከአንጋጫ ወረዳ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ #ያለው ፤ በ23/08/2012 ከኬንያ በሞያሌ በኩል ከተመለሰው ታማሚ ጋር ንክኪ ያለውና አሁን በአንጋጫ ለይቶ ማቆያ ያለ።

በአጠቃላይ በክልሉ የኮሮና ቫይረስ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ከጤና ሚኒስቴር በተገለጸው መሰረት ቁጥር 4 (አራት) መድረሱን የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ አስታውቋል።

(ደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ/ መንግስት ጤና ቢሮ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AtoAknawKawza

ከደቡብ ክልል ጤና ቢሮ የተሰጠ መረጃ ፦

በደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ/ መንግስት በ2 ዞኖች ማለትም ወላይታ /ቦዲቲ/ እና ጉራጌ/ቡታጅራ/ በለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በደቡብ ህብረተሰብ ጤና ላብራቶሪ በተደረገው 34 የላብራቶሪ ምርመራ 2 (ሁለት) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። ቫይረሱ የተገኘባቸው ሁለቱም ሰዎች በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ፡፡

የዕለቱ ታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ ፦

ታማሚ 1 - የ20 ኢትዮጵያዊት ፣ ከቦዲቲ ወረዳ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላት ፤ ከሞያሌ የተመለሰችና በቦዲቲ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለች።

ታማሚ 2 - የ50 ዓመት ኢትዮጵያዊ ፤ ከቡታጅራ ወረዳ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ #የሌለው ፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ያለው ግንኙነት በመጣራት ላይ ሲሆን ለሌላ ህክምና ሆስፒታል መጥቶ በነበረው ምልክት መነሻ ናሙና ተወስዶ የተረጋገጠ።

በደቡብ ክልል ቫይረሱ የተገኘባቸው አጠቃላይ ሰዎች ከጤና ሚኒስቴር በተገለጸው መሰረት 6 (ስድስት) መድረሱን የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ አስታውቋል።

(ደ/ብ/ብ/ህ/ክ/ መንግስት ጤና ቢሮ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#AtoAknawKawza

በደቡብ ክልል እስከ 12 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች በኮቪድ - 19 ቫይረስ ሊጠቁ ይችላሉ ሲል የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ #አስጠንቅቋል

የቢሮው ሃላፊ አቶ አቅናው ካውዛ እንዳሉት የከፋ የተጋላጭ ሁኔታ አመልካች እንደሚያሳየው አሁን በበሽታው ዙሪያ የሚያታየውን 'የጥንቃቄ ጉድለት' መቅረፍ ካልተቻለ በክልሉ 60 በመቶ የሚሆነው ነዋሪ በቫይረሱ ሊጠቃ ይችላል።

📹#DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AtoAknawKawza

ዛሬ በፌደራል ደረጃ በወጣው መግለጫ በደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መ አራት (4) ሰዎች ከኮቪድ-19 ማገገማቸው መገለፁ ይታወሳል።

የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ባወጣው መግለጫ ያገገሙት አራቱ ታማሚዎች ከወላይታ ዞን ፣ ከስልጤ ዞን ፣ ከከምባታ ጠምባሮ ዞን ፣ ከሀላባ ዞን መሆናቸውን አሳውቋል።

አራቱም (4) ግለሰቦች በተደረገላቸው ምርምር ከቫይረሱ ነፃ መሆናቸው የተረጋገጠ ሲሆን በተቀመጠው መመሪያ መሰረት ከዚህ በኃላ 14 ቀናት በቤታቸው ራሳቸውን ለይተው መቆየት እንደሚገባቸው በማስገንዘብ ወደ ቤተሰቦቻቸው ተመልሰዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 46 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ! ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 3,410 የላብራቶሪ ምርመራ አርባ ስድስት (46) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 701 ደርሷል፡፡ ቫይረሱ የተገኘባቸው 29 ወንድ እና 17 ሴት ሲሆን የዕድሜ ክልላቸው ከ12 እስከ 79 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት 45 ሰዎች ኢትዮጵያውያን…
#AtoAknawKawza

በደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መ በኮቪድ-19 መያዛቸው ከተረጋገጠ ሰባት (7) ሰዎች መካከል ስድስቱ (6) በተደረገላቸው ህክምና ከበሽታው አገግመዋል።

ዛሬ በፌደራል ደረጃ በተሰጠው መግለጫ በደቡብ ክልል ሁለት (2) ሰዎች ማገገማቸው መገለፁ ይታወሳል።

እኚህ ያገገሙት ታማሚዎች ከጉራጌ ዞን (ቡታጅራ ወረዳ) እና ከሃዲያ ዞን (ሻሸጎ ወረዳ) መሆናቸውን የክልሉ ጤና ቢሮ ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
TIKVAH-ETHIOPIA
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 95 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል! ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 5,034 የላብራቶሪ ምርመራ ዘጠና አምስት (95) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 1,063 ደርሷል፡፡ ቫይረሱ የተገኘባቸው 71 ወንድ እና 24 ሴት ሲሆን የዕድሜ ክልላቸው ከ15 እስከ 80 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት 94 ሰዎች…
#AtoAknawKawza

በደቡብ ክልል በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች 8 መሆናቸው ተገልጿል!

ባለፉት 24 ሰዓት በደ/ብ/ብ/ህ/ክ መንግስት 100 ያህል የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጓል። በአጠቃላይ በክልሉ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር ስምንት (8) ነው።

አንድ ግለሰብ ከአዲስ አበባ ቤት ለቤት በተደረገው ምርመራ ፖዘቲቭ ሆኖ ወደ ሲዳማ ዞን በንሳ ወረዳ ከገባ በኃላ ሲያዝ በዛሬው ዕለት የጤና ሚኒስቴር አዲስ በቫይረሱ መያዛቸውን ካረጋገጠው 95 ሰዎች ውስጥ አንዱ ሲሆን በንሳ ወረዳ ላይ ተይዞ በይርጋለም ለይቶ ማቆያ እንዲቆይ ተደርጓል።

ከግለሰቡ ጋር ንክኪ የነበራቸው እና አብረውት ከአዲስ አበባ ወደ በንሳ የመጡ 14 እና 20 ሰዎች ደግሞ ከተጠርጣሪውና ከእነሱ ጋር ንክኪ ያላቸው ተለይተው በድምሩ 34 ሰዎች ንክኪ ያላቸው #በይርጋለም ለይቶ ማቆያ ውስጥ ይገኛሉ።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AtoAknawKawza በደቡብ ክልል በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች 8 መሆናቸው ተገልጿል! ባለፉት 24 ሰዓት በደ/ብ/ብ/ህ/ክ መንግስት 100 ያህል የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጓል። በአጠቃላይ በክልሉ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር ስምንት (8) ነው። አንድ ግለሰብ ከአዲስ አበባ ቤት ለቤት በተደረገው ምርመራ ፖዘቲቭ ሆኖ ወደ ሲዳማ ዞን በንሳ ወረዳ ከገባ በኃላ ሲያዝ በዛሬው ዕለት የጤና…
#AtoAknawKawza

ትላንት ከተገለፀው 1 ሰው በተጨማሪ ሌሎች አምስት (5) ሰዎች ከአዲስ አበባ ውጤታቸው ሳይገለፅ ወደ ሲዳማ ዞን መግባታቸውን የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ አሳውቋል።

እነዚህ 5 ግለሰቦች ትላንት በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) መያዛቸው ከተረጋገጠ 95 ሰዎች መካከል ናቸው።

እስካሁን ባለው መረጃ ከአምስቱ (5) ግለሰቦች መካከል ሶስቱ (3) ተይዘዋል። ሁለቱ (2) ወደመኖሪያ አካባቢያቸው ከገቡ በኃላ አንደኛው ጥቁር ውሃ ላይ ነው የተያዘው።

በአሁን ሰዓት ሁለቱ (2) ይርጋለም ማከሚያ ማዕከል ውስጥ ይገኛሉ፤ አንደኛው ሀዋሳ ማከሚያ ማዕከል ውስጥ ነው የሚገኘው።

ከግለሰቦቹ ጋር ንክኪ እንዳላቸው የተለዩ ሰዎች ተይዘዋል። በንሳ ላይ 141 ሰዎች፣ ይርጋለም ላይ 180 ሰዎች፣ ሀዋሳ ከተማ 90 ሰዎች በአጠቃላይ 411 ሰዎች ተይዘዋል።

ሁለቱ ያልተገኙት ሰዎች እስካሁን እየተፈለጉ ነው። አንደኛው ሽፋ ወረዳ ዕድሜው 18 የሆነና ሌላኛው በንሳ ዳዬ ዕድሜው 23 የሆነ ወጣት ናቸው #እየተፈለጉ የሚገኙት።

@tikvahethiopia @tikvahethiopia