TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#attention አሁንም በአንዳድን የማንቡክ አካባቢዎች የተኩስ ድምፅ እንደሚሰማ እየተገለፀልን ከቤተሰቦቻችን እየተገለፅልን ነው። በአካባቢው የተፈጠረውንና እየተፈጠረው ያለውን ዝርዝር ጉዳይ ከቤተሰቦቻችን ጠይቀን፤ ተጨማሪ መረጃዎችን አካተን እንድታነቡት እናደርጋለን። ለሁሉም ግን የሚመለከታችሁ አካላት [የፀጥታ ኃይሉ] የአካባቢውን ደህንነት እንድታስጠብቁ የቲክቫህ ማንቡክ ቤተሰቦች አሳስበዋል።…
የማንቡክ ከተማ ሰላም መደፍረስ...

[በሸገር ኤፍ ኤም 102.1]

- ለማንቡክ ከተማ ፀጥታ መደፍረስ መነሻው ከቀናት በፊት የተፈፀመን ግድያ ተከትሎ በሌሎች ሁለት ሰዎች ላይ የተፈፀመ የበቀል ግድያ እንደሆነ ነዋሪዎች ገልፀዋል።

- የበቀል ጥቃት የተፈፀመባቸው ወገኖችም አፀፋውን ለመስጠት ትናንት ረፋድ ላይ መሳሪያ ታጥቀው ወደማንቡክ ከተማ መጥተው ነበር። በመከላከያ ኃይል ምክር ወደመጡበት ተመልሰው ነበር።

- እኚሁ ሰዎች አመሻሽ ላይ በከተማው ድርቻ ላይ በሚገኙ መኖሪያ ቤቶች ላይ ጥቃት ፈፅመዋል። በጥቃቱም በከተማው ዳርቻ ያሉ ቤቶች በእሳት ጋይተዋል። ከመከላከያ ሰራዊት ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ከጥቃት ፈፃሚዎቹ መካከል የተወሰኑ ሰዎች ተገድለዋል።

- የመተከል ዞን ምክትል አስተዳዳሪ የፀጥታ መደፍረስ ምክንያቱ እውነት እንደሆነ አረጋግጠዋል። ችግሩ መከሰቱንም አምነዋል። ምክትል አስተዳዳሪው የሰው ህይወት መጥፋትን በተመለከተ ማጣራት እየተደረገ ነው ብለዋል። የተወሰኑ የሳር ቤቶችም ተቃጥለዋል ሲሉ ገልፀዋል። መከላከያ ገብቶ ሁሉንም ነገር አረጋግቷል።

#ShegerFM #ማህሌትታደለ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia