TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#university

የኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነባርና አዳዲስ ተማሪዎቻቸውን መቀበል ጀምረዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲዎቹ ካለፉት ጊዜያት በተለዬ ተማሪዎቻቸውንና ወላጆቻቸውን ውል አስገብተው ነው እየተቀበሉ የሚገኙት፡፡ የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ አዳዲስ ተማሪዎቹን መቀበል ጀምሯል፤ ሠላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ አጠናቅቆ ተማሪዎችን መቀበል መጀመሩን ነው ዩኒቨርሲቲው ያስታወቀው፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ችሎት

በነአቶ በረከት ስምዖን የክስ መዝገብ ዛሬ ከሰዓት በኋላ የተሰየመው ችሎት ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን ተጨማሪ ሰነድ መርምሮ የሰነዱ አካል እንዲሆን ብይን ሰጥቷል፡፡ ከፍርድ በፊት የሚቀርብ ማንኛውም ማስረጃ መርምሮ ትክክለኛ ብይን ለመስጠት አጋዥ ስለሚሆን ዐቃቤ ሕግ እንዲያዝለት ያቀረበውን 141 ገፅ ማስረጃ ከዚህ ቀደም የቀረበው የሰነድ ማስረጃ አካል እንዲሆን ሊያያዝ ይገባል ብሏል ፍርድ ቤቱ፡፡ ፍርድ ቤቱ ሰነዱን መርምሮ ብይን ለመስጠትም ለጥቅምት 21 ቀን 2012 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert

ከሰኔ 15 ጥቃት ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በማረፊያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን ሲከታተሉ የነበሩት ብርጋዲዬር ጄኔራል ተፈራ ማሞ፣ ኮሎኔል አለበል አማረ እና ኮሎኔል ባምላኩ እያንዳንዳቸው በአስር ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲለቀቁና ጉዳያቸውን በውጭ ሆነው እንዲከራከሩ መወሰኑን የአማራ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል፡፡

Via #AMMA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#attention በደቡብ ወሎ ዞን "ቃሉ ወረዳ" የተከሰተው የአንበጣ መንጋ በሰብል እና እንስሳት መኖ ላይ እያደረሰ ይገኛል። ጉዳዩ የሁሉንም ትኩረት ይሻል። #AMMA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
- ተጠርጣሪዎችን አፈላልጎ በመያዝ እርምጃ እንደሚወሰድ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ!

በምሥራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ከተማ አስተዳደር በቤተ እምነት ተቋማት ላይ የደረሰው የቃጠሎ አደጋ በተመለከተ የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን መግለጫ ሰጥቷል፡፡

በትናንትናው ዕለት ታኀሣሥ 10 ቀን 2012 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡20 አካባቢ በሞጣ ከተማ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የእሳት ቃጠሎ መከሰቱን ተከትሎ በሌሎችም የሃይማኖት ተቋማት ላይ የእሳት ቃጠሎ መፈጸሙን ከዞኑ ፖሊስ መምሪያ ያገኙትን መረጃ ጠቅሰው የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ማኅበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል መምሪያ ኃላፊ ጀማል መኮንን ተናግረዋል፡፡ በቡድን በመሰባሰብ መስጂዶች ላይ ጥቃት እንደተፈፀመ ነው ኮማንደር ጀማል የተናገሩት፡፡

በድርጊቱ በሞጣ ከተማ አስተዳደር ቀበሌ 03 የሚገኝ መስጂድ ሙሉ በሙሉ ሲቃጠል፣ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን እና ቀበሌ 05 እና 06 የሚገኙ መስጂዶች ደግሞ በከፊል እንደተቃጠሉና አንድ የገበያ ማዕከል በቃጠሎና በመሰባበር ጉዳት እንደደረሰበት ኮማንደር ጀማል መኮንን ተናግረዋል፡፡

በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት ሪፖርት እንዳልተደረገም አመላክተዋል፡፡ ፖሊስ ችግሩን በማስቆም የማረጋጋት ሥራ እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በቀጣይ ተጠርጣሪዎችን አፈላልጎ በመያዝ እርምጃ እንደሚወሰድም አስታውቀዋል፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች ሃይማኖትንና ማንነትን መሠረት አድረገው የሚነሱ ችግሮችን ኅብረተሰቡ ከማባባስ ይልቅ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በመተባበር የማርገብና የማረጋጋት ልምድ ሊዳብር እንደሚገባ ኮማንደር ጀማል መኮንን መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

https://telegra.ph/AMMA-12-21

#AMMA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

በደሴ ከተማ አስተዳደር ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ የእምነቱ ተከታዮች በሞጣ ከተማ በእምነት ተቋማት ላይ ደረሰው ጥቃት አሳፋሪ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የእምነቱ ተከታዮች በደሴ ከተማ በሚገኘው ዐረብ ገንዳ መስጂድ ባደረጉት ውይይት አጥፊዎቹ በሕግ ሊጠየቁ እንደሚገባም ጠይቀዋል፡፡ ጥቃቱ ከመድረሱ በፊትም ሆነ ከደረሰ በኋላ መንግሥት እያሳዬ ያለው ለዘብተኛ አቋም መታረም እንደሚገባውም አሳስበዋል፡፡

የክልሉ መንግሥት በመስጂዶች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እንደሚደርስ መረጃዎች እንደነበሩት በማንሳትም ቅድመ መከላከል አልሠራም በሚል ወቅሰዋል፡፡ ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላም በቁጥጥር ሥር ያዋላቸው ተጠርጣሪዎች ቁጥር አነስተኛ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

መንግሥት የተቃጠሉ ቤተ እምነቶችን እንዲሠራና የተዘረፉ ንብረቶችን እንዲመለሱ ማድረግ እንደለበትም ተናግረዋል፡፡ችግሩ እንዲባባስም ሆነ የቤተ እምነቶች እንዲቃጠሉ የሚዲያ አካላት ድርሻ ከፍተኛ እንደሆነም ነው ተወያዮቹ ያነሱት፡፡ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ሚዲያ አውታሮች በተለይ በመስጂዶች ላይ ጥቃት ሲደርስ የሚሰጡት ሽፋን ሚዛናዊ እንዳልሆና መታረም እንደሚገባውም መክረዋል፡፡ መንግሥት የተቃጠሉ ቤተ እምነቶችን እንዲሠራና የተዘረፉ ንብረቶችን እንዲያስመልስም አሳስበዋል።
#AMMA

#TIKVAH_ETH

በሞጣ ከተማ በእምነት ተቋማት ላይ የተፈፀመው ድርጊት የሚያወግዙ ሰልፎች በተለያዩ ከተሞች እና አካባቢዎች እንደተደረጉ መረጃዎች ደርሰውናል። በባሌ ደሎ መና በተካሄደ ሰልፍ የሙስሊሙ እና ክርስትያኑ ማህበረሰብ አባላት ድርጊቱን አደባባይ በመውጣት በጋራ አውግዘዋል። በተለያዩ ከተሞች እና አካባቢዎች የተደረጉ የተቃውሞ ሰልፎችን ማስፈንጠሪያውን በመጫን መመልከት ትችላላችሁ https://telegra.ph/TIKVAH-12-22

@tikvahethiopiaBot
ወደ ጎንደር 19 ተጨማሪ በረራዎች ተዘጋጅተዋል...

የጥምቀት በዓልን ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ - ጎንደር ተጨማሪ የበረራ መርሃ ግብሮችን ማዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡ እስካሁን ድረስ ጥር 8/2012 ድረስ በአጠቃላይ ወደ ጎንደር የሚደረጉ 19 ተጨማሪ በረራዎች መዘጋጀታቸውን ነው አየር መንገዱ የገለፀው። ለጥምቀት በዓልና ተያያዥ ጉዳዮች በቀጥታ ወደ ጎንደር የሚያመሩ 2 ሺህ 500 የሚደርሱ መንገደኞች መመዝገባቸውም ተመላክቷል፡፡

#AMMA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የጥምቀት በዓል ታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ...

የጥምቀት በዓልን ጨምሮ ሌሎች ቅርሶችን በዓለም ቅርስነት ማስመዝገብ ብቻ ሳይሆን መንከባከብ እንደሚገባ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ አሳስበዋል፡፡

የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴ በንግግራቸው መጀመሪያ ጎንደር ወጣቶች ለበዓሉ ድምቀት እያደርጉት ላለው ቀና ትብብር እና በጎ ፈቃደኝነት አመሥግነዋል፡፡ የጥምቀት በዓል በዩኔስኮ በማይዳሰስ ቅርስነት በመመዝገቡ ማግስት ጎንደር ተገኝተው በማክበራቸው መደሰታቸውንም ፕሬዝዳቷ ገልጸዋል፡፡

#AMMA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ሜጀር ጀነራል ነስረዲን አብዲ ጎንደር ገብተዋል!

የገደሪፍ ዋና አስተዳዳሪ ሜጀር ጀነራል ነስረዲን አብዲ ለጉብኝት ጎንደር ገብተዋል። የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ማስተዋል ስዩም ለአስተዳዳሪው አቀባበል አድርገውላቸዋል።

"ሜጀር ጀነራሉ ወደ ኢትዮጵያ ስመጣ ሀገሬ ውስጥ ያለሁ ያህል ይሰማኛል" ብለዋል። በቆይታቸውም በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ያለውን ግንኙነት በሚያጠናክሩባቸው ዙሪያ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል። በወረታ ደረቅ ወደብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ምረቃ ላይ አስተዳዳሪው የሚሳተፉ ይሆናል።

#AMMA
@tikvahethiopia @tikvahethioiaBot
ዶክተር ፋንታ ማንደፍሮ የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር ሆነው ተሾሙ!

የአማራ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት 5ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን አስቸኳይ ጉባኤ ላይ ሰፊ ክርክር ከተደረገ በኃላ ምክር ቤቱ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እንዲሆኑ የቀረበውን የፋንታ ማንደፍሮ/ዶ/ር/ን ሹመት አፅድቋል፡፡

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ተመሥገን ጥሩነህ የዕጩ ተሿማዎችን ለምክር ቤቱ አባላት ሲያቀርቡ እንዳሉት ወቅቱን የዋጀ በዕውቀት ላይ የተመሠረተ አመራር ለመስጠትና ኃላፊነትን በአግባቡ ለመወጣት የሚጠይቅ ወቅት ላይ በመሆናቸው ሹመቱ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

#AMMA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የዐብይ ፆም ወቅትን በተመለከተ መግለጫ ተሰጠ!

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበር ተክለሃይማኖት አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ የዐብይ ጾም ወቅትን አስመልከቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

ብጹእነታው በመግለጫቸው እንዳሉት ምዕመናን የዘንድሮውን ጾም ሲከውኑ ከጥላቻ እና ቂም ራሳቸውን በማራቅ እና በጾም ወቅት ከጥላቻና ዛቻ፣ ከበቀልና ተንኮል ርቀው መሆን አንዳለበት አሳስበዋል፡፡

‹‹እጃችንም፣ እግራችንም፣ አፋችንም ዓይናችንም፣ ጆሯችንም፣ ውስጣችንም በመንፈሳዊ ሕይወት አሸብርቀን መጾም ይገባናል፡፡ በዚህ ወቅት መስማትና ማዳመጥ ያለብን እግዚአብሔርን ብቻ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ድምጽ ፍቅርና ሠላም በመሆኑ አንድነትና ስምምነት፣ ዕርቅና ይቅርታ ፍትሕና እውነት፣ እኩልነትና ኅብረት በማድረግ ለሀገር ሠላም በመጸለይ ሊሆን ይገባል›› ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ሁኔታ እንድትወጣ ምዕመኑ በጾምና ጸሎት በአንድ ልቦና ለሀገሩ ሠላም እና ዕድገት፣ ፍትሕ እና እውነት በመቆም ጾሙን መከወን እንደሚገባቸውም ብጹእነታቸው አሳስበዋል፡፡

#AMMA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ADDISABABA

‹‹የአማራ አብሮነት እሴቶች ለኅብረ-ብሔራዊ አንድነት›› በሚል መሪ ሐሳብ የተለያዩ አካላት በተገኙበት በአዲስ አበባ ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡

የአማራ ክልል የበይነ መንግሥታት ቢሮ ኃላፊ ደስታ ተስፋው (ዶክተር) ‹‹አማራ የመቻቻልና የመከባበር እሴት ያለው አቃፊ ሕዝብ ነው፤ እውነታው ይህ ቢሆንም በተዛቡ ትርክቶች ምክንያት እንደጨቋኝ መታየቱ ተገቢ አይደለም›› ብለዋል፡፡

ዶክተር ደስታ አብሮነት እና ጠንካራ ኅብረ-ብሔራዊ አንድነት ለመፍጠር መሠራት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡

በመድረኩም የአማራ የአብሮነት እሴቶችና ተሞክሮዎች፣ የተሳሳቱ ትርክቶች ያስከተሏቸው ችግሮችና የመፍትሔ ሐሳቦች ውይይት ይደረግባቸዋል፡፡

#AMMA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia