TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#NobelPeacePrize

የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የ2019 የሰላም የኖቤል ሽልማት በማሸነፋቸው የእንኳን ደስ አልዎት መልእክት አስተላልፏል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የተሸለሙት የኖቤል የሰላም ሽልማት ሀገሪቱ የጀመረችው የሰላም ጉዞን አጠናክሮ ለመቀጠል እንደሚያስችል እምነቱን ገልጿል።

Via ትግራይ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወይዘሮ ፅዮን ተክሉ ለTIKVAH-ETH በላኩት መልዕክት ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የ2019 የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ መሆናቸውን በማስመልከት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር እና በ "እኛ ለእኛ" የኢትዮጵያውያን በጎ ፍቃደኞች መርሃ ግብር ስም የእንኳን ደስ ያልዎት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
ወ/ሮ ፅዮን ተክሉ - የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ! #NobelPeacePrize

#TikvahEthiopia
#NobelPeacePrize

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ኡመር ኢድርስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የኖቤል የሰላም ሽልማት በማግኘታቸው የእንኳን ደስ አልዎት መልዕክት አስተላፉ፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ኡመር ኢድሪስ ለFBC እንደተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ የሰሯቸዉ ስራዎች ከዚህም በላይ ሊያስመሰግኗቸውና ሊያሸልሟቸው የሚችሉ በመሆናቸው ኮርተንባቸዋል ብለዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ትልቅ ሽልማት የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ መሆን ነው ያሉት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ኡመር በዚህም መላዉ የኢትየጵያ ህዝብ ደስ ሊለው እንደሚገባ ገልፀዋል። ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ኡመር ኢድሪስ መልካም ተግባር መስራት ምን ያህል አስፈላጊና ተጽእኖ መፈጥር እንደሚችል ማሳያ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሽልማት ያሳያል ብለዋል።

Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ "የኖቤል የሰላም ሽልማት" በማሸነፋቸው የሀገራችንን ስም በዓለም መድረክ ከማስጠራት ባለፈ 918,000 የአሜሪካ ዶላር በገንዘብ፣ የወርቅ ሜዳልያ እንዲሁም ዲፕሎማ ይሸለማሉ!!

#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን የሰላም የኖቤል ሽልማት በማስመልከት በነገው ዕለት በመላ ኦሮሚያ የደስታ መግለጫ ሰልፎች የሚደረጉ መሆኑን የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኖቤል የሰላም ተሸላሚ መሆናቸውን ተከትሎ ባስተላለፉት የደስታ መልዕክት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኤርትራ ጋር ሰላም እንዲኖር አድርገዋል ብለዋል፡፡ ዶ/ር ቴድሮስ ኢትዮጵያዊ በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል ብለዋል፡፡

Via EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ የኖቤል ሽልማት በማሸነፋቻው በበርካታ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች የደስታ መግለጫ ሰልፎች በመደረግ ላይ ይገኛሉ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize

ዱከም፣ ገላን፣ ሻሸመኔ፣ አምቦ፣ ወሊሶ፣ ሱሉልታ፣ ባሌ ሮቤ፣ ጅማ፣ መቱ፣ በደሌ፣ ባቱ፣አዳማ፣ ጉጂ ዞን፣ ቦረና ዞን፣ እኔ ሌሎች በርካታ ከተሞች የደስታ ሰልፎች እየተደረጉ ናቸው።

Via EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ መሆናቸውን ተከትሎ በተለያዩ ከተሞች የደስታ መግለጫ ሰልፎች ተደርገዋል፦ ዱከም፣ ገላን፣ ሻሸመኔ፣ አምቦ፣ ወሊሶ፣ ሱሉልታ፣ ባሌ ሮቤ፣ ጅማ፣ መቱ፣ በደሌ፣ ባቱ፣አዳማ፣ ጅማ ዞን /ጌራ/፣ ድሬዳዋ፣ ቢሾፍታ፣ ሰበታ፣ ለገጣፎ ለገዳዲ፣ ሀረር፣ጭሮ፣አሶሳ/ቤኒሻንጉል ጉምዝ/ ደንገሃቡር/ሱማሌ ክልል/

@tsegabwolde @tikvahethiopia