TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አረጓዴ_አሻራ Cooperative Bank of Oromia S.C staff #BISHOFTU
#ጀግኒት

ተማሪ ZEHARA #ከBAHIRDAR 615፣ HILANI ከአዳማ #ODA_SPECIAL_BOARDING 606፣ NEBUS #ከBISHOFTU 607 በዘንድሮው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ/የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና ያስመዘገቡ እንስቶች ናቸው! #ኢትዮጵያዊት

#BAHIDAR
#BISHOFTU
#ODA_SPECIAL_BOARDING

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከቢሾፍቱ የአይን እማኝ...

"ከኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን መንገድ ላይ ስንደርስ ያልተፈቀደ አርማ ያለበትን ልብስ ለብሳችኃል/ይዛችኃል/ በሚል አታልፉም አሉን/የፀጥታ አካላት/። አረንጓዴ ቢጫ ቀይ የለበሱም ነበሩ እሱን እንዲህ ሆነን ማለፍ እንደማንችል ተነገረን። መዘምራንም ጭምር። ይሄን አርማ ይዛችሁ እና ለብሳችሁ ማለፍ አትችሉም አሉን። እዛው የነበርነው ሰዎች እንደዛ ከሆነ እዛው ኪዳነ ምህረት እናበራለን ብለን ተመለስን። ወደኪዳነ ምህረት ስንመለስ ወደአዳባባይ የሄዱት ሰዎች አንድ ደብር ጎሎ #አናበራም ብለው ሁሉም ተሰብስቦ ወደ ኪዳነ ምህረት እየተመለሰ ነበር #አደባባይ ያለውን ሳያበሩ ቀርተው። ግማሹ ኪዳነ ምህረት ከሄደ በኃላ እላይ ያለውን ወደታች እንዳይወርድ ታች ያለውን ወደ ላይ እንዳይወጣ ከለከሉ። ሰዎች ወደቤት አንሄድም አሉ። ሰዎችን አሳምነውም ወደአደባባይ ለመውሰድ እና ደመራው እንዲበራ ለማድረግ ጥረት አድርገው ነበር ግን ሰው አልተስማማ። እየዘመርን ወደቤታች እንመለሳለን ብሎ እኛ ወደቤታችን ሄደናል።"

ቢሾፍቱ ስለተፈጠረው ጉዳይ ምላሽ ለማግኘት ጥረት አድርጌ ነበር አልተሳካም። #BISHOFTU #ቢሾፍቱ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቢሾፍቱ በልምምድ ላይ የነበረ አንድ የኢትዮጵያ የጦር አውሮፕላን ተከስክሶ የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል። አውሮፕላኑ ዛሬ ጠዋት ቢሾፍቱ ከሚገኘው የአየር ሃይል ካምፕ በመነሳት በልምምድ ላይ እያለ በምስራቅ ሸዋ ዞን አደአ ወረዳ ኡኬ ደንካካ በተሰኘ ቦታ መከስከሱን የምስራቅ ሸዋ ዞን ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አበራ ያሚ ለዶቸ ቨለ አረጋግጠዋል። በአደጋው የሁለት አብራሪዎች ህይወት ማለፉንም አቶ…
#RIP

ሻለቃ ሰበሪ ቶፊቅ🕯ሻምበል ኃየሎም ተስፋይ!

#BISHOFTU

በአደጋው በደረደበት ወቅት ኢንስትራክተር አብራሪ ሻለቃ ሰብሪ ቶፊቅ ከተዋጊ ጄቱ ተስፈንጥሮ የወጣ ቢሆንም፣ ፓራሹቱ ሊዘረጋለት ባለመቻሉ ሕይወቱ እንዳለፈ ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል። ሌላው በአደጋው ሕይወቱን ያጣው ሠልጣኝ አብራሪ ሻምበል ኃየሎም ተስፋይ ነው፡፡

ሻለቃ ሰብሪ በ1999 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ አየር ኃይል የበረራ ትምህርት ቤት በከፍተኛ ማዕረግ እንደተመረቀና አየር ኃይሉን ከአሥር ዓመት በላይ እንዳገለገለ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ድሬዳዋ ተወልዶ ያደገው ሻለቃ ሰብሪ በጂማ ዩኒቨርሲቲ የኢንጂነሪንግ ተማሪ የነበረ ቢሆንም፣ ለበረራ በነበረው ፍቅር የምሕንድስና ትምህርቱን አቋርጦ ወደ አየር ኃይል የበረራ ትምህርት ቤት እንደገባ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ በትምህርቱም በከፍተኛ ውጤት ያስመዘግብ እንደነበር ገልጸው፣ ሲመረቅ ከክፍሉ በአንደኛ ደረጃ እንዳጠናቀቀ ተናግረዋል፡፡ ሻለቃ ሰብሪ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነበር፡፡

ሱኮይ 27 ተዋጊ አውሮፕላኖች የተገዙት በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ነበር!

Via Reporter
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Bishoftu

ሀገር መከላከያ ሰራዊት በከተማይቱ ከትላንት ጀምሮ የተፈጠረውን አለመረጋጋት ለመቆጣጠር ጥረት እያደረገ ይገኛል። በሌላ በኩል በዛሬው ዕለት በቢሾፍቱ ከተማ የሰው ህይወት ላይ ጉዳት ደርሷል። ዝርዝር መረጃዎችን ስናገኝ የምን ቅርብ ይሆናል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#BISHOFTU

የቢሾፍቱ መንገድ እንደተከፈተ የቢሾፍቱ ቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ገልፀዋል። በየመንገዱ ላይ ያሉት ድንጋዮች ሙሉ በመሉ ስላልተነሱ አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉም መክረዋል። የማዘጋጃ ጽዳቶች የትናንት የተቃጠሉ ጎማዎችን ከአስፓልት ላይ እያጸዱ ናቸው። የንግድ ቤቶች፣ ሆቴሎች ግን አሁንም እንደተቀዛቀዙ ናቸው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#BISHOFTU

ከቡዛየሁ ታደለ ፋውንዴሽንና ከኢስት አፍሪካን ላየን ብራንድስ ማኑፋክቸሪንግ የተላከ መልዕክት!

ብዙአየው ታደለ ፋውንዴሽን ከኢስት አፍሪካን ላየን ብራንድስ ማኑፋክቸሪንግ ጋር በመሆን በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ ማህበረሰብ እና ልዩ እርዳታ ለሚፈልጉ የቢሾፍቱ ከተማ ወገኖቻችን ለተከታታይ 60 ቀናት የሚቆይ የቁርስ፣ የምሳ፤ የእራት ምገባ ፕሮግራም የከተማው ከንቲባ እና የድርጅቶቹ የስራ አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ሚያዝያ 5፣ 2012 ዓ.ም ተጀምሯል። ፈጣሪ አለማችንን ፣ ኢትዮጵያን ይጠብቅልን፡፡ ከተባበርን ይህም ያልፋል!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Bishoftu

ዛሬ ቢሾፍቱ በሚገኘነው የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኮሌጅ የባህር ኃይል አርማ፣ የትከሻ ምልክትና የደንብ ልብስ ይፋ ተደርጓል።

በሥነሥርዓቱ ላይ የመከላከያ ጠ/ኤታማዥር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ፣ የባህር ኃይል ዋና አዛዥ አድሚራል ክንዱ ገዙና ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገራት አታሼዎችና ከፍተኛ የጦር መኮንኖች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

አርማው ቀይ፣ ነጭና ቢጫ ቀለማትን ሲይዝ፣ ቀዩ መስዋእትነት እና ዝግጁነትን ፣ ነጩ ሰላም ፣ እውቀት፣ ላብና የመለያ ክብርን እንዲሁም ቢጫው ለሀገርና ለህዝቦች መጪው ጊዜ የብሩህ ተስፋ ዘመን መሆኑን የሚያመላክት መሆኑ ተገልጿል።

በአርማው ላይ የባህር ኃይል ዓለምአቀፍ ምልክት የሆነው መልህቅ እና በቀላሉ የማይበገር የባህር ኃይል በተሰማራበት ቀጠና ላይ የሚሰጠውን ግዳጅ በብቃትና በጥንካሬ እንደሚወጣ የሚያሳየው የወይራ ዘለላ ተቀምጦበታል።

በአርማው ላይ ያለው ሰማያዊ መደብ ባህር ኃይሉ ተልዕኮውን የሚወጣው በባህርና በውቅያኖስ ላይ መሆኑን ሲያሳይ ሰንደቅ አላማው ደግሞ ለሀገርና ለሰንደቅ አላማ ዘብ መቆምን ያሳያል ተብሏል።

ዛሬ ይፋ የተደረገው የባህር ኃይል አርማ በጠቅላይ መምሪያው ፣ በመርከቦች እና በተለያዩ የህትመት ውጤቶች ላይ ጥቅም ላይ እንደሚውል መገለፁን የኢዜአ ዘገባ ያስረዳል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ADAMA #BAHIRDAR ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት መጠነ ሰፊ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራውን በባሕር ዳር እና በአዳማ ከተሞች ጀምሯል። ይህ የደንበኞች ሙከራ ከድሬዳዋ፣ ሐረር እና ሐረማያ በመቀጠል የሳፋሪኮምን ኔትወርክ ለመሞከር ባሕር ዳርን እና አዳማን 4ኛ እና 5ኛ የኢትዮጵያ ከተሞች አድርጓቸዋል። የሲም ካርድ ሽያጭ ምዝገባ፣ የአየር ሰዓት እና የስልክ ቀፎዎች ግዢ እንዲሁም የደንበኞች…
#Bishoftu #Mojo #Debrebrihan

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት መጠነ ሰፊ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራውን በቢሾፍቱ፣ ሞጆ እና ደብረ ብርሃን ከተሞች መጀመሩን አሳውቋል።

ይህ የደንበኞች ሙከራ የሳፋሪኮምን ኔትወርክ እየሞከሩ ያሉትን ከተሞች ቁጥር #ስምንት የሚያደርሰው ሲሆን ባለፉት ሦስት ሳምንታት ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ ሐረማያ፣ ባሕር ዳር እና አዳማ ላይ ሙከራው መጀመሩ ይታወቃል።

ደንበኞች የሲም ካርድ ሽያጭ ምዝገባ፣ የአየር ሰዓት እና የስልክ ቀፎዎች ግዢ እንዲሁም የደንበኞች ድጋፍ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መለያ ከተለጠፈባቸው መደብሮች እና ሱቆች ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ፦

#ቢሾፍቱ 📍

በቢሾፍቱ ሁለት የሳፋሪኮም መለያ የተለጠፈባቸው መደብሮች (ከኦዳ ነቤ ሆቴል ጎን እና ከመዘጋጃው ፊትለፊት)፤

#ሞጆ📍

በሞጆ አንድ መናኸሪያ አካባቢ የሚገኝ የሳፋሪኮም መለያ የተለጠፈበት መደብር፤

#ደብረብርሃን 📍

ከዘርዕ ያዕቆብ አደባባይ ወረድ ብሎ ባለው ኖክ ማደያ አካባቢ የሚገኝ የሳፋሪኮም መለያ የተለጠፈበት መደብር ደንበኞችን ለማገልገል ክፍት መሆኑን ገልጿል።

በቢሾፍቱ፣ በሞጆ እና በደብረ ብርሃን ከተሞች አገልግሎት በሚጀምረው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሙከራ ኔትወርክ ደንበኞች ዳታ መጠቀም፣ ጥሪዎች እና የጽሁፍ መልዕክቶችን ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ከኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ጋር መለዋወጥ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ጥሪዎችን ማድረግ እንደሚችሉ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አሳውቆናል።

#SafaricomEthiopia

@tikvahethiopia
" ፍትህን እስከምናገኝ ድረስ የሚከፈለውን መስዋዕትነት እንከፍላለን " - ካውንስሉ

በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ከርስቲያን ኩሪፍቱ ማዕከል ላይ የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ኢ-ህገ መንግስታዊ ጥሰት እየፈጸመ እንደሆነ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስትያናት ካውንስል አሳወቀ።

ድርጊቱን በመቃወምም መግለጫ አውጥቷል።

ካውንስሉ ፤ የኩሪፍቱ ማዕከል በህጋዊ መንገድ ለቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ ሰነድ ያለው ይዞታ መሆኑን ገልጿል።

የከተማ አስተዳደሩ ግን ከቤተ ክርስቲያኒቱን ቦታ ላይ 40 ሺህ ካሬ ሜትር የሚሆነውን በኃይል ለሁለት ለግለሰቦች በመስጠት ኢ ህገመንግስታዊ በደል እንደፈጸመ ጠቁሟል።

ይህንን ጉዳይ አስመልከቶ ከዚህ ቀደም ቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳዩን ለፍርድ ቤት አቅርባ ፍርድ ቤት ቦታው የቃለ ሕይወት ይዞታ መሆኑን ውሳኔ አስተላልፎ ነበር።

የከተማ አስተዳደሩ የግንባታን ሂደት ሆን ብሎ እያስተጓጎለ ስለነበረ ጉዳዩን ለሚመለከታቸው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና ለፌደራል መንግስት ቀርቦ በከፍተኛ አመራር ደረጃ ኮሚቴ ተዋቅሮ እየታየ ባለበት ሁኔታ ትላንት ሐምሌ 3 ቀን 2016 ዓ.ም የከተማ አስተዳደሩ የቤተ ከርስቲያቱ ይዞታ ውስጥ ወታደሮችን እና የመሬት አስተዳደር ባለሙያዎችን ይዞ በመግባት ችካል በማስቀመጥ የቤተ ከርስቲያኒቱን ይዞታ ለግለሰብ በማስተላለፍ ህገ ወጥ ተግባር እንደፈጸመ ካውንስሉ በይፋ አሳውቋል።

ሁኔታው ከባድ እና በወንጌላውያን አምነት ተከታዮች ላይ የተቃጣ ሐይማኖታዊ ጥላቻ ባላቸው ግለሰቦች የተቀነባበረ እንደሆነ ካውንስሉ አመልክቷል።

ጥያቄው ልማት ከሆነ ለምን ቤተ ክርስቲያኒቱ እንድታለማ ቅድሚያ አይሰጣትም ? የሚለው ሐሳብ ላይ መግባባት ኖሮ ቤተ ከርስቲያኒቱ ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ ሙሉ በሙሉ ጊቢውን ወደ ልማት በመቀየር እየሰራች እንደነበር ተጠቁሟል።

ይህ በሆነት ሁኔታ ነው ለአመታት በይዞታነት የያዘችውን ንብረት በሐይል በመቀማት የተወሰደው።

ካውንስሉ ፤ " የወንጌል አማኞች በዚህ የህልውናችን ጉዳይ ህግ መንግስታዊ መብታችን እስከሚከበር ድረስ ለሚመለከታቸው ለክልሉ እና ለፌደራል መንግስት አካላት ጥያቄያችንን ከማቅረብ ባሻገር ፍትህን እስከምናገኝ ድረስ የሚከፈለውን መስዋዕትነት እንከፍላለን " ሲል አሳውቋል።

#Bishoftu

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update! " መሬቱ ጭራሽ በNGO እጅ ገብቶ አያውቅም ከመጀመሪያው ጀምሮ የቤተ ክርስቲያኗ እጅ የነበረ ነው " - ቤተ ክርስቲያኗ የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን 40 በመቶ የሚሆነው የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር " በጉልበት ሊወስደው ነው " ስትል በተደጋጋሚ መግለጿ ይታወቃል። ለቤተ ክርስቲያኗ ቅሬታ ምላሽ እንዲሰጥ ቲክቫህ ትላንት የጠየቅነው የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር…
" የሚዲያ ዘመቻችሁን እንድታቆሙ እንጠይቃለን " - የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር

የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ፥ " በሕገ-ወጥ መንገድ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይለማ የቆየ 280,000 ካሬ ሜትር ለልማት እንዲውል ማድረግ ሕገ- መንግስትን ማስከበር እና ማክበር እንጂ የሚያስወቅስ ጉዳይ አይደለም " አለ።

ይህን ያለው ዛሬ ባወጣው ማሳሰቢያ ነው።

አስተዳደሩ ፥ " ሕግ እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን ማስከበር የአንድ የመንግስት አካል ሃላፊነት ሆኖ እያለ ለ40 ዓመታት ያለ ልማት ( ያለ ህዝብ ጥቅም) የቆየ 280,000 ካሬ ሜትር ስኩዌር (የህዝብ እና የቀጣይ ትውልድ ውስን ሐብትን በሕገ -ወጥ መንገድ በየትኛውም መንገድ በሚዲያ ጫናም ሆነ በጉልበት ይዞ መገኘት ወንጀል ነው " ብሎታል።

" በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ኩሪፍቱ ሃይቅ ዙርያ የሆነው እንደሱ ነው " ሲል አክሏል።

ከተማ አስተዳደሩ ፥ " የመንግስት እና የሀዝብ ውስን ሃብትን የመጠበቅ ፥የማስተዳደር እና ለልማት እንዲዉል የማድረግ ህዝባዊ ፣ መንግስታዊ ግዴታ እና ተጠያቂነት አለበት " ያለ ሲሆን " ተደጋግሞ የሚደረግብን የሚዲያ ጥላቻ እና ዘመቻ የህዝብን ጥቅም ከማረጋጋጥ ጉዞዋችን ቅንጣት የማይገታን መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን " ብሏል።

" የከ/መስተዳድሩ ይህን መሬት ለልማት እንዳያውል በሃይማኖት ሽፋን ሕገ- ወጥ ሁከት እና ዘመቻ እያደረጋችሁ ያላችሁ አካላት በሙሉ ከድርጊታቸሁ እንድትታቀቡ " ሲልም አሳስቧል።

" ከዚህ ውጪ የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ ላይ የሕግ-የበላይነት ለማስከበር እንገደዳለን " ሲልም አስጠንቅቋል።

" የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ይህንን ተረድተዉ የተጀመረውን ሃገራዊ እና የሕዝቦችን ተጠቃሚነት ጉዞ የሚያደናቅፍ የሚዲያ ዘመቻውን እንድያቆምልን እንጠይቃለን " ብሏል።

#Bishoftu

@tikvahethiopia