TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አምባሳደር መለስ አለም...

ዛሬ #በናይሮቢ መድኃኒያለም ቤተ ክርስትያን ባለፈው ሳምንት ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ በመብረር ላይ ሳለ #ቢሾፍቱ አቅራቢያ በተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ቦንግ 737 ሕይወታቸውን ላጡ መንገደኞች የመታሰቢያ ፀሎት ስነ ስርዓት ላይ አምባሳደር #መለስ_አለም ተገኝተው ንግግር አድርገዋል። በፀሎት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ሰፋ ያለ ንግግር ያደረጉት አምባሳደር #መለስ የአውሮፕላኑ አደጋ በደረሰበት ዕለት ወደ ናይሮቢ እንደመጡና #በተከሰከሰው አውሮፕላን #ሊሳፈሩ እንደነበርም ተናግረዋል።

Via BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ድርድር ካለፉት ሳምንታት ጀምሮ መንግስት ከTPLF ጋር ድርድር ሊያደርግ እንደሆነ የተለያዩ ምንጫቸው በግልፅ ያልተገለፁ/ ያልተረጋገጡ መረጃዎች ሲወጡ ነበር። ዛሬ ከህ/ተ/ም/ቤት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ የሰጡት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ድርድርን በተመለከተ መረጃ ሰጥተዋል። " ከማንም ጋር ሰላም ነው የምንፈልገው። " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ ፤ " እያንዳንዷ የሰላም ቀን ለእኛ ትርፍ ታስገኝልናለች።…
#ድርድር

የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት በሰላም መቋጫ ያገኝ ዘንድ የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑ ይታወቃል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህም አንዳንድ የውጭ ሀገር ሚዲያዎች ድርድርን በተመለከተ በግልፅ ምንጫቸው የማይታወቁ መረጃዎችን ሲያሰራጩ ከርመዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት እስካሁን ንግግር አለመጀመሩን ነገር ግን ለዚሁ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁሟል።

ትላንት ፓርላማ የቀረቡት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በይፋ የታወቀ አጥኚ ኮሚቴ ተቋቁሞ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካኝነት እየተመራ መሆኑን፤ እስካሁን ውጤቱን አለማሳወቁን እና የሚደራደረው ኮሚቴም ይሄ መሆኑን ጠቁመው ነበር። ድርድር ሲጀመር መንግስት የሚደብቀው ነገር እንደሌለም ገልፀው ነበር።

ይህ የጠቅላይ ሚስትሩ ንግግር ከተሰማ ብዙም ሳይቆይ በህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የተፃፈ ደብዳቤ ተሰራጭቷል።

ይኸው ደብዳቤ ህወሓት በኬንያ መንግስት በተጠራ ድርድር የሚሳተፍ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ለመላክ መዘጋጀቱን ይገልጻል።

ደብዳቤው በኬንያ መንግስት የተጠራ ድርድር #በናይሮቢ ስለመኖሩ ፍንጭ የሰጠ ነው።

ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሰላም ድርድሮችን በማስመልከት የትግራይ ክልልን አቋምን ለማሳወቅ ደብዳቤውን የፃፉት ለአፍሪካ ህብረት የወቅቱ ሊቀ መንበርና የሴናጋሉ ፕሬዝዳንት ማኪ ሳል፣ ለኬንያው ፕሬዝዳንት አሁሩ ኬንያታ፣ ለተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ፕሬዝዳንት ሼክ ሞሃመድ ቢን ዛይድ አልናህያን እና ለታንዛኒያዋ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን እንዲሁም የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝን ጨምሮ ለተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ነው።

ያንብቡ ; https://telegra.ph/Dr-Debretsion-GMicahel-06-15

@tikvahethiopia