TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በአዳማ ከተማ 1 በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው ተገኘ!

በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ አንድ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው መገኘቱን በክልሉ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የተቋቋመው ግብረ ሃይል ገለጸ፡፡

ከግለሰቡ ጋር ንክኪ የነበራቸው 24 ሰዎች ተለይተዋልም ነው የተባለው። ግብረ ሃይሉ በህብረተሰቡና በተቋማት የሚታየው ቸልተኝነት አሁንም #አሳሳቢ ነው ብሏል።

#FBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር ሀገር አቀፍ መረጃዎች፦

- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ሥራ እንዲውል የአንድ ወር ደመወዛቸውን ለግሰዋል።

- ሼህ ሁሴን አሊ አላሙዲ የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ወረርሽኝን ለመግታት የ120 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርገዋል። በተጨማሪ የሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ማኔጅመንት፣ አመራር እና ሠራተኞች ከ10 ሚልዮን ብር በላይ ለተመሳሳይ አላማ አበርክተዋል።

- የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ 14, 000 ሰራተኞቹን በጊዚያዊነት ከስራ አሰናብቷል። ሰራተኞቹ ከስራ የተሰናበቱት በአሜሪካና በአውሮፓ ገበያዎች የምርቶቹ ዋነኛ ተቀባይ የነበሩት ድርጅቶች በኮሮና ምክንያት የገበያ ፍላጎታቸው እየተቀዛቀዘ በመምጣቱ ነው።

- መከላከያ ሰራዊት ነገ በአዲስ አበባ የቫይረሱን ስርጭትን ለመግታት የሚያግዙ መልዕክቶችን የያዙ በራሪ ወረቀቶችን በሄሊኮፕተር ይበትናል፡፡ በተጨማሪም የተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ በማርሽ ባንድ የታጀበ የማንቂያ ቅስቀሳ ያደርጋል፡፡

- አልማ የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ መመደቡን አስታውቋል።

#DW #etv #EliasMeseret #fbc #ena
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ADDISABABA

የፐብሊክ ሰርቪስ ድርጅት ከረቡዕ ጀምሮ ተሳፋሪዎች የአፍ መሸፈኛ ጭንብል በአስገዳጅነት እንዲጠቀሙ ሊደርግ መሆኑን አስታውቋል።

ከረቡዕ ጀምሮ የአፍ መሸፈኛ ጭምብል የማይጠቀሙ ተሳፋሪዎችን እንደማይጭንም ገልጿል።

በተጨማሪ የትራንስፖርት እጥረትን ለመፍታት የመጫን አቅምን ከአስገዳጅ የአፍ መሸፈኛ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ወደ 43 የሚያድግ ይሆናል ተብሏል - #FBC

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

በአዲስ አበባ ከመጭው ዓርብ (ሚያዚያ 30/2012 ዓ/ም) ጀምሮ የሚኒባስ ተጠቃሚዎች የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎችን #በአስገዳጅነት እንዲጠቀሙ ሊደረግ መሆኑ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ባለስልጣን እንዳለው ተሳፋሪዎች የትራንስፖርት አገልግሎት ለመጠቀም ሲንቀሳቀሱ ጭምብሎችን መጠቀም ይኖርባቸዋል ብሏል። ባለስልጣኑ ተሳፋሪዎች ያለ አፍ መሸፈኛ ጭምብል ታክሲ መጠቀም አይችሉም ሲል ገልጿል - #FBC

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FicheChambalala

ፊቼ ጫምባላላ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ስርጭትን ለመከላከል በአደባባይ እንዳይከበር የሲዳማ የሀገር ሽማግሌዎች ወስነዋል። የሲዳማ የሀገር ሽማግሌዎች/አያንቶዎች በዓሉ ግንቦት 12 እና 13 ተከብሮ እንዲውልም ቀን ቆርጠዋል።

ወረርሽኝ፣ ጦርነት እና ርሀብ እንዲሁም የታላቅ ሰው ህልፈት ሲከሰት ፊቼ ጫምበላላ በዓል በአደባባይ የማይከበር መሆኑ ታሪካዊ አመጣጥ ያለው መሆኑን የገለፁት አያንቶዎቹ በዓሉ የኮቪድ 19 ስርጭትን ለመከላከል ዘንድሮ አደባባይ እንዳይከበር ወስነዋል፡፡

በኮሮና ወረርሽኝ አማካኝነት ሊከሰት የሚችለውን ችግር ከግምት ውስጥ በማስገባት በታላቁ (ሶሬሳ) ጉዱማሌም ሆነ በወረዳ እና በቀበሌ ደረጃ በዓሉን በአደባባይ ማክበር የማይቻል እንደሆነም የሀገር ሽማግሌዎች ገልፀዋል።

#fbc
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#ATTENTION

የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ኤባ አባተ የኮሮና ቫይረስ ከተገኘባቸው 365 ሰዎች 56ቱ የውጭ ሃገር የጉዞ ታሪክም ሆነ ከበሽታው ተጠቂ ግለሰብ ጋር ንክኪ #ያልነበራቸው መሆናቸውን አሳውቀዋል።

ከእነዚህ ውስም 48 በመቶ ' በአዲስ አበባ ከተማ ' ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎች በመሆናቸው ህብረተሰቡ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባው አሳስበዋል።

#FBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19Ethiopia

በአምቦ ዩኒቨርስቲ የተቋቋመው የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ማእከል ተመርቆ ስራ ጀምሯል። ይህ ላብራቶሪ በቀን እስከ 1 ሺህ ናሙናዎችን መመርመር እንደሚችል ተገልጿል።

በተጨማሪ የአርባ ምንጭ የኮቪድ-19 ምርመራ ማዕከል ምርመራ ጀምሯል። ማዕከሉ በቀን እስከ 400 የሚደርሱ ናሙናዎችን የመመርመር አቅም አለው። ማዕከሉ ለጋሞ፣ ጎፋ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ኮንሶ ፣ እና ከደራሼ ዞኖች፣ ቡርጂ፣ አማሮ እና አሌ ልዩ ወረዳዎች ለሚመጡ ናሙናዎች የ24 ሰዓታት የምርመራ አገልግሎት ይሰጣል - #FBC

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#GERD

የታላቁ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት የግድቡን ተፈጥሯዊ የግንባታ ሂደት በጠበቀ መልኩ የሚከናወን መሆኑን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ዛሬ በሰጡት መግለጫ መናገራቸውን #FBC ዘግቧል።

ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ ሲሰራጭ የነበረው የውሃ ሙሌቱን የሚያሳዩ የሳተላይት ምስሎች ትክክለኛና እውነተኛ መሆናቸውንም ለሚዲያዎች አረጋግጠዋል።

ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያ ፣ ሱዳን እና ግብጽን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሃገራት የተሳተፉበት የ11 ቀን ውይይት በተወሰኑ ነጥቦች ላይ በ3ቱ ሀገራት መካከል መግባባት ላይ መደረሱን አስረድተዋል።

ከዚህ ባለፈ ግን በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ በኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅም ላይ ተፅዕኖ የሚኖራቸው ነጥቦች ላይ ጥንቃቄ ማድረግ በማስፈለጉ ልዩነት እንደነበርም በሰጡት መግለጫ አንስተዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#GERD

የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ መሪዎች በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ዛሬ ይመክራሉ።

የዛሬው ውይይት ሰኔ 19 የተካሄደውን ውይይት ተከትሎ የሚካሄድ መሆኑ ነው የተገለፀው።

የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር እና የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ስሪል ራማፎሳ በቪዲዮ ኮንፈረንስ የሚካሄደውን ስብሰባ ይመሩታል ተብሎ ይጠበቃል።

በስብሰባው ላይ የቢሮው አባላት የሆኑት የዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ኬንያ እና የማሊ መሪዎች እና ተወካዮችም ይሳተፉበታል።

የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ በዛሬው ስብሰባው ኢትዮጵያ ፣ ሱዳንና ግብፅ በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ሲያደርጉት በነበሩት የሶስትዮሽ ድርድር የደረሱበትን ደረጃ የሚመለከት ይሆናል - #FBC

@tikvahethiopiaBot @tsegabwolde
ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ዝርዝር ፦

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከዛራ የካቲት 27 እስከ መጋቢት 30 ቀን 2013 ዓ/ም የሚቆይ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ መዘጋጀቱን አስታውቋል።

በዚሁ መሰረት የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ይፋ አድርጓል።

- ቤንዚን በሊትር 25 ብር ከ 86 ሳንቲም፥

- ኤታኖል ድብልቅ ቤንዚን በሊትር 25 ብር ከ 36 ሳንቲም፥

- ነጭ ናፍጣ በሊትር 23 ብር ከ18 ሳንቲም፥

- ኬሮሲን በሊትር 23 ብር ከ18 ሳንቲም፥

- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 20 ብር ከ27 ሳንቲም፥

- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 19 ብር ከ78 ሳንቲም፥

- የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 38 ብር ከ65 ሳንቲም ይሆናል ብሏል ሚኒስቴሩ።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተደረገውን የዋጋ ማስተካከያ በተመለከተ በዝርዝሩ የተካተቱ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫን ለማሳወቅ የህዝብ ማስታወቂያ ዛሬ ይፋ እንደሚያደርግ ገልጿል።

በዚሁ መሰረት #በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች በሚገኙ ማደያዎች ተግባራዊ ይደረጋል ብሏል። #FBC

@tikvahethiopia