TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አዲስ አበባ‼️

ሜድሮክ ፒያሳ አካባቢ ያጠረውን ጨምሮ በመዲናዋ ለዓመታት ያለስራ ታጥረው የተቀመጡ ቦታዎችን አጥር #የማፍረስ ስራ ነገ በይፋ ይጀመራል።

በነገው እለት አጥር የማፍረስ ስራ ከሚጀመርባቸው ውስጥ ሜድሮክ ኢትዮጵያ ፒያሳ አካባቢ ለግዙፍ የገበያ ማእከል ግንባታ ከተረከበው በኋላ ለዓመታት አጥሮ ያቅመጠው ቦታ አንዱ ነው።

ሜድሮክ ፒያሳ አካባቢ ያለውን ስፍራ ለልማት ከተረከበ በኋላ ያለምንም ስራ ከ20 ዓመት በላይ አጥሮ ማስቀመጡም አይዘነጋም።

በተጨማሪም በመዲናዋ በተለያዩ አካባቢዎች በልማት ስም መሬት ከወሰዱ በኋላ ሳያለሙ ለበርካታ ዓመታት ታጥረው የተቀጡ መሬቶች ላይ ያሉ አጥሮችም ከነገ ጀምሮ መፍረስ ይጀምራሉ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለረጅም ጊዜ ታጥረው በቆዩ ቦታዎች ንብረታቸውን በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ባላነሱት ላይ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን ተከትሎ ነው አጥሮቹ የሚፈርሱት።

የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማት ማኔጅመንት ፅህፈት ቤት የደንብ ማስከበር ፅህፈት ቤት ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በጋራ በመሆን እርምጃ መውሰድ የጀመሩት።

አስተዳደሩ ባልለሙ ቦታዎች ላይ ንብረቶቻቸውን ያስቀመጡ አካላት ንብረታቸውን እንዲያነሱ ከሳምንት በፊት መግለጫ መስጠቱ የሚታወስ ነው።

ይሁን እንጅ እነዚህ አካላት ንብረቶቻቸውን ማንሳት ባለመጀመራቸው ምክንያት አስተዳደሩ ወደ እርምጃ የገባው።

አስተዳደሩ የህዝብን ሃብት ለተገቢው ልማትና ለነዋሪዎች ተጠቃሚነት እንዲውል በጀመረው ተግባር ህገ ወጥነትን እንደማይታገስና፥ ህግ የማስከበር ሃላፊነቱን እንደሚወጣ መግለጹም ይታወሳል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray በናይሮቢው የሰላም ስምምነት ሰነድ ላይ ፊርማቸውን ያኖሩት የትግራይ ኃይሎች አዛዥ ጄነራል ታደሰ ወረደ በናይሮቢው ስምምነት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ባለፉት ቀናት ለኃይሎቻቸው ኦረንቴሽን ሲሰጥ እንደነበር እና ይኸው ኦረንቴሽን በቀጣይ ሁለት ቀን እንቀሚያልቅ ገልፀዋል። ይህን የገለፁት በክልሉ ለሚገኙት የመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ ነው። ጄኔራል ታደሰ ወረደ ምን አሉ ? " በናይሮቢው…
#Update #Peace

በሰላም ስምምነቱ መሰረት የትግራይ ታጣቂዎች በስራቸው ከነበሩ የውግያ ግምባሮች ለቀው መውጣት እንደጀመሩ ተገልጿል።

ታጣቂዎቹ ከደቡብ ፣  ማይ ቅነጣል፣ ዛላምበሳ፣ ነበለት ፣ ጨርጨር ፣ ኩኩፍቶ ፣ ሕጉምብርዳ ፣ በሪተኽላይ እና አበርገለ ለቆ ግንባሮች ነው መውጣት እንደጀመሩ ከክልሉ መገናኛ ብዙሃን የተሰማው።

ከጥቂት ቀናት በፊት ጄነራል ታደሰ ወረደ (የትግራይ ኃይሎች አዛዥ) በሰጡት መግለጫ በናይሮቢው ስምምነት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ለኃይሎቻቸው ኦረንቴሽን ሲሰጥ እንደነበር እና ይኸው ኦረንቴሽን እንዳለቀ ኃይላቸው ካለበት ቦታ Disengage አድርጎ / ተላቆ የውጊያ ግንባሮች #የማፍረስ እና ሰራዊቱ ወደ ተቀመጠለት ቦታ እንደሚጓጓዝ መግለፃቸው አይዘነጋም።

ጄነራል ታደሰ ፤ " የሎጅስቲክስ አቅማችን ወይም የማጓጓዝ አቅማችን እስከፈቀደ ድረስ በአንድ ጊዜም ልናነሳው እንችላለን ምናልባት የተወሰኑ ቀናት ሊወስድ ይችላል " ማለታቸውም የሚወስ ነው።

@tikvahethiopia