TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ኒውዮርክ

የተመድ ዐመታዊ ጠቅላላ ጉባዔ በኒውዮርክ ጀምሯል፡፡ መሪዎች ዛሬ ስለ አየር ንብረት ለውጥ ይመክራሉ፡፡ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ለሁለተኛ ጊዜ በጉባዔው አልተገኙም፡፡ ለጉባዔው ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴንና ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ገዱ አንዳርጋቸውን ነው የወከሉት፡፡

ምንጭ፦ wazemaradio
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸የኢፌዴሪ ፕሬዘዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕና ባለቤታቸው ሜላኒያ ትራምፕ! #ኒውዮርክ #US
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #Afar #Amhara " ለሰላም ተስፋ አለ " የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ምክትል ዋና ፀሀፊ አሚና መሀመድ ዛሬ ስለኢትዮጵያ ጉብኝታቸው መግለጫ ሰጥተዋል። በጦርነቱ የተጎዱትን ትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎችን ከጎበኙ በኋላ ለሰላም ተስፋ እንዳለ የገለጹ ሲሆን " በእርግጥ የሚስተዋለው ከጥቂት ወራት በፊት ከነበሩ ግጭቶች ያነሰ ነው " ብለዋል። ከትግራይ ክልል አመራሮች፣…
#USA , #NewYork📍

" በሰማሁት ታሪክ እንባዬን መቆጣጠር አቅቶኛል " - አሚና መሀመድ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ምክትል ሃላፊ አሚና መሃመድ የኢትዮጵያ ግጭት በሴቶች ላይ ባደረሰው ከባድ ጉዳት እጅጉን መደንገጣቸውን ገለጹ፡፡

ምክትል ዋና ጸሃፊዋ ይህንን ያሉት ለ5 ቀናት #በኢትዮጵያ
- በትግራይ ክልል
- አማራ ክልል
- አፋር ክልል
- ሶማሌ ክልል ያደረጉትን ጉብኝት በማስመለክት ትላንት በ #ኒውዮርክ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው፡፡

አሚና የትግራይ ክልል ግጭት ባስከተለውን አስከፊ መዘዝ የተጎዱቱን የኢትዮጵያ ሴቶች አግኝተው ማነጋገረቻውን እና በሰሙትም ታሪክ እንባቸው መቆጣጠር እንዳቃታቸው ገልጸዋል፡፡

አሚና ግጭት ባለባቸው የኢትዮጵያ ክልሎች ያሉት ሴቶች " ሊታሰብ የማይቻል አሰቃቂ አደጋ አጋጥሞቸዋል " ብለዋል።

በተለይ በጦርነቱ ወቅት አስገድዶ መድፈር የተፈጸመባቸውን ታሪክ ማድመጥ ኩፉኛ የሚያምና የሚያስለቅስ ጉዳት መሆኑን ገልፀዋል። " ኢትዮጵያውያን ሴቶች ሊታሰብ በማይቻል መልኩ ተጎድተዋል " ብለዋል አሚና መሐመድ።

በልጆቻቸው ፊት ከተደረፈሩት ባሻገር የደረሰባቸውን ጉዳት የማያስታውሱ ሴቶችን ጭምር ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

አሚና መሀመድ ፤ በትግራይ አንዲት በተደጋጋሚ በቡድን የተደፈረች፣ በዚህም ወንድ ልጅ የወለደችና አሁን ላይ የቤተሰቦቿንና ማህበረሰቡ አይን ማየት ተስኗት ራሷን አግላ የምትገኝ እንስት አግኝተው አሳዛኝ ታሪክ መስማታቸውን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር የአብሮነት ጉዞ ነበር ያሉት አሚና " ተመድ በተለይ ለሴቶች እና ህጻናት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ማገገም አስቸኳይ የሰብአዊ ድጋፍ ቅድሚያ መስጠቱን ይቀጥላል " ሲሉ በትዊተር ገፃቸው ላይ ፅፈዋል።

በጦርነቱ ከተጎዱት ሴቶች ባሻገርም የኢትዮጵያን ጦርነት በተመለከተ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፣ ፕሬዝዳንት እንዲሁም ደግሞ ከትግራይ ክልል መሪዎች ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውን ተናግረዋል።

" ለተፈጸመው ግፍ ሁሉም ተጠያቂ ነው " ያሉት አሚና " አንድ አካል በሌላው ላይ እንዲህ ማድረጉ ፍጹም ተቀባይነት የለውም " ሲሉ ገልፀዋል።

በኢትዮጵያ ሴቶች ላይ ለተፈጸመው ሁሉ " ያለ ጥርጥር ፍትህ እና ተጠያቂነት ሊረጋገጥ ይገባል" ሲሉ ተናግረዋል።

ሁሉም ተፋላሚ ወገኖች ሳይታረቁና ተጠያቂ ካልሆኑ ዘላቂ ሰላም ማምጣት እንደማይችል አስረግጠው ተናግረዋል።

(አል ዓይን ኒውስ)

@tikvahethiopia
#USA #RUSSIA

አሜሪካ #ኒውዮርክ መቀመጫው ባደረገው የተመድ ዋና መስሪያ ቤት ይሰሩ የነበሩትን 12 ሩሲያውያን ዲፕሎማቶች አባራለች።

በተመድ የአሜሪካ ሚስዮን እንዳስታወቀው ከሆነ የሩስያ ዲፕሎማቶቹ "ለሀገራዊ ደህንነታችን ጠንቅ የሆኑ የስለላ ስራዎችን ሲሰሩ የነበሩ የመረጃ ሰዎች" ናቸው ሲል ገልጿል። እርምጃ ለበርካታ ወራት የተደረገውን ጥናት መሰረት በማድረግ የተወሰደ ነው ብሏል።

እርምጃው የተወሰደው በተመድ ዋና መ/ቤት ስምምነትና አሰራር መሰረት እንደሆነ ተነግሯል።

በተመድ የሩሲያ አምባሳደር ቫሲሊ ኔቤንዝያ ዲፕሎማቶቹ እስከ መጋቢት7/22 ድረስ አሜሪካን ለቀው እንዲወጡ መጠየቃቸውን አረጋግጧል፡፡ አሜሪካ በዲፕሎማቶቹ ላይ ለወሰደችው እርምጃ “ሩሲያ ተገቢውን ዲፕሎማሲያዊ ምላሽ ትሰጣለች” ብለዋል።

መረጃውን ሮይተርስን ዋቢ አድርጎ ያሰራጨው አል ዓይን ኒውስ ነው።

@tikvahethiopia