TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Peace

የሰላም ስምምነቱን በተመለከተ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ከሃይማኖት ተቋማት እና ሲቪክ ማህበራት ጋር ውይይት አድርገው ነበር።

በዚህ ውይይት ላይ ምን አሉ ?

- የሰላም ስምምነቱ #የህዝብ ፍላጎትን መሰረት ያደረገ ነው ብለዋል።

- የሰላም ስምምነቱ ፤ ከፍተኛ የሆነ ችግር ላይ ያለውን ህዝብ ለማዳንና ህዝቡ መሰረታዊ አገልግሎቶችን እንዲጠቀም ሰላም እንዲያገኝ ለማድረግ የተደረሰ መሆኑን ገልፀው ሌሎች ጉዳዮች በህገመንግስት መሰረት ፖለቲካዊ መፍትሄ የሚፈለግላቸው መሆኑን ገልፀዋል። ስምምነቱ ከምንም በላይ ተኩስ የማቆም ጉዳይ ነበር ሲሉ ተናግረዋል።

- የተደረሰው  የሰላም  ስምምነት  ተግባራዊ እንዲሆን እየተሰራ ባለበት በዚህ ወቅት ላይ አሁንም የኤርትራው ፕ/ት ኢሳያስ አፈወርቂ ኃይል በህዝቡ ላይ ከፍተኛ ግፍ እየፈፀመ፣ ንብረት እየዘረፈ ፣ እያወደመ መሆኑና ስምምነቱ እንዲደናቀፍ እየሰራ እንደሆነ ገልፀው የፌዴራል መንግስት የህዝቡን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነበት ስላለበት ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

- በስምምነቱ መሰረት ሰብዓዊ እርዳታ እና መድሃኒት እየገባ መሆኑን ተናግረዋል። " ስምምነቱ ላይ ድጋፍ በአቸኳይ እንዲገባ የሚል ነገር ነበር በወቅቱ ወዲያው የገባ ድጋፍ አልነበረም አሁን ግን ቀስ በቀስ የሚገባው ሰብዓዊ ድጋፍ እየጨመረ ነው " ብለዋል። እህል እና መድሃኒት ይዘው የሚገቡ ተሽከርካሪዎች እየጨመሩ መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ደብረፅዮን ፤ ዓለም አቀፍ እርዳታ አቅራቢዎች በሙሉ ወደ እንቅስቃሴ ገብተዋል ብለዋል።

- ወደ ክልሉ ከሚገባው የሰብዓዊ እርዳታ ጋር በተያያዘ በስምምነቱ መጀመሪያ ሰሞን ላይ አስፈላጊው ስራ በጊዜ ስላላለቀ እና ባለመዘጋጀቱ ወደ ትግበራ እንዳልተገባ አሁን ላይ ግን ሁሉም ዝግጁ መሆኑን ፣ የሚያደናቅፍ ነገር እንደሌለው ፣ በመንገድ ላይ የነበረው በርካታ ፍተሻና የቁጥጥር ጣቢያዎች አሁን መስተካከሉን ተናግረዋል።

- ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ፤ " የተቋረጡት መሰረታዊ አገልግሎቶች መልሰው አልተከፈቱም " ያሉ ሲሆን " በኛ በኩል ሙሉ ዝግጅት አድርገናል #ባንክ#ቴሌኮም እንዲጀምር ፤ የኤሌክትሪክ ኃይል ባለን አነስተኛ አቅም እየተጠቀምን ብንቆይም መስተካከል ያለባቸው ነገሮች መስተካከል አለባቸው። በፌዴራል አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ እያንዳንዳቸው ተፈትሸው ስራ ለመጀመር ምን ያስፈልጋቸዋል  ?  የሚለው ተጠንቷል። አገልግሎት ወደ ነበረበት ለመመለስ ሙሉ ዝግጅት ተደርጓል ፤ አሁን የሚቀረው ስርዓት አስይዞ ከፌዴራል አገልግሎት ሰጪ አካላት ጋር በመነጋገር በቅደም ተከተል ማስፈፀም ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
" ይህ የተለየ የቪፒኤን አይነት ነው " - ኢትዮ ቴሌኮም

ኢትዮ ቴሌኮም በሞባይል ቪ.ፒ.ኤን (VPN) ጥቅል አገልግሎቱ ላይ የዋጋ ማሻሻያ በማድረግ እንዲሁም ያለተገደበ አማራጭን አካቶ ማቅረቡን ገለፀ።

ድርጅቱ ፤ በቪ.ፒ.ኤን (VPN) አገልግሎቱ ደህንነቱ በተጠበቀ የዳታ አገልግሎት #የድርጅት አገልግሎት ማሳለጥ፣ #ቢሮዎችን እርስበእርስ ማገናኘት እንዲሁም በየትኛውም ቦታ የድርጅት መረጃ እና መሳሪያዎች በመጠቀም ቢዝነስ ማከናወን የሚያስችል ነው ብሏል።

ደንበኞቹ ፤ አገልግሎቱን ለማግኘት በአቅራቢያቸው የሚገኝ የድርጅት አገልግሎት መስጫ ማዕከሎችን መጎብኘት እንደሚችሉ ጠቁሟል።

ነገር ግን ድርጅቱ የዋጋ ማሻሻያውን በሚመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ ገፆቹ ያሰራጨው መረጃ በርካቶችን ጋር ያጋባና " VPN ምንድነው ? " ብለው እንዲጠይቁ አድርጓል።

በኢትዮጵያ ውስጥ ወራትን ካስቆጠረው የማህበራዊ ሚዲያዎች #ገደብ ጋር የሚገናኝ የመሰላቸውም ብዙ ናቸው።

ለመሆኑ ቪ.ፒ.ኤን (VPN) ምንድነው ?

(ኢትዮ ቴሌኮም)

ቪ.ፒኤ.ን (VPN) ማለት የግል እና የመንግስት ተቋማት ከተለያዩ ቅርንጫፎቻቸው ጋር እንዲገናኙ የሚያደርግ ነው።

ተቋማቱ የራሳቸውን የግል ኔትወርክ እንዲያደራጁ ያስችላቸዋል፤ መረጃን ለማጋራት እንዲሁም በቅርንጫፎች ውስጥ ያሉትን ሁሉንም የመረጃ ቴክኖሎጂ ስርዓቶችን በመደበኛ ወይም በተንቀሻቃሽ አማራጮች መተግበር ያስችላል።

አገልግሎቱ የሞባይል ኔትዎርክ ሽፋን ተደራሽ በሆነባቸው እና የዳታ አገልግሎትን በሚሰጡ በሁሉም ኢትዮጵያ ክፍሎች ይገኛል።

ኢትዮ-ቴሌኮም የቪፒኤን አገልግሎቶች በሁለት አማራጭ የሚያቀርብ ሲሆን እነዚህም " የሞባይል ብሮድባንድ ቪፒኤን " እና " የፊክስድ ብሮድባንድ ቪፒኤን " ናቸዉ፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ድርጅቱ " ይህ የተለየ የቪፒኤን አይነት ነው። " ያለ ሲሆን " የተንቀሳቃሽ ስልክ ኔትዎርክ ሽፋን ባለባቸው አካባቢዎች ነገርግን ግን መደበኛ ባለገመድ መስመር ተደራሽነት ባሌለባቸው አካባቢዎች ልክ እንደ #ባንክ ያሉ የድርጅት ደንበኞች ቅርንጫፎቻቸውን ደህንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ ለማገናኘት የሚረዳ የግል መዳረሻ አውታር ሆኖ እንደ አማራጭ የቀረበ ነው።  " ሲል አስረድቷል

የሞባይል ቪፒኤን / VPN / ጥቅል ዋጋ ማሻሻያ የሚመለከተውም ይሄን ነው ብሏል።

Credit : #EthioTelecom

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከእንግዲህ በሽፍትነት / rebel በመሆን መንግሥትን መጣል አይደለም ፤ መነቅነቅ አይቻልም " - ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ " ከእንግዲህ በኃላ በሽፍትነት / rebels በሚመስል ነገር መንግስትን መጣል አይደለም መነቅነቅ እንኳን አይቻልም " አሉ። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ይህን ያሉት በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ከፍተኛ እና ታማኝ ግብር ከፋይ ባለሀብቶችን ሰብሰበው በመከሩበት ወቅት ነው።…
" በቅርቡ 5 ሚሊዮን ዶላር ከውጭ በአንድ ባንክ ተልኮ ይዘናል " - ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ሁለት ቦታ (ከመንግስት ጋር እና ጫካ መንግስትን ለመጣል ከሚታገሉ ጋር) የሚጫወቱ አንዳንድ ባለሃብቶች አሉ ሲሉ ተናገሩ።

ይህን የተናገሩት ከታማኝ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ጋር ምክክር ባደረጉበት ወቅት ነው።

ባለሃብቶቹ በምክክር መድረኩ ስለ #ሰላም ጉዳይ ያነሱ ሲሆን ጠ/ሚስትሩም ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠ/ሚኒስትሩ ፤ " ሰላም ተብሏል እውነት ነው አስፈላጊ ነው " ብለዋል።

" ድሮ ሀብታሞች አዝማሪ ቀጥረው ያጫውቱ ፣ ይገጠምላቸው ነበር ድሃው እራት እየበላ በግጥም ይተባበራል ፤ አሁን ድገሞ ሀብታሞች #ዩትዩበር ይቀጥራሉ ድሃው በላይክ እና ሼር ይተባበራቸዋል እነዚህ ሰዎች እንደፈለጉ ሲያተረማምሱ ይውላሉ " ሲሉ ተናግረዋል።

" ዩትዩበሮቹን ባንቀልብ ወደ ስራ ወደ ኢንድስትሪ ይገቡ ነበር ፤ ለዚህ አስተዋጽኦአችን ምንድነው ብሎ ስራ ፈጣሪው ባለሃብቱ ግብር ከፋዩ ቢያስብ ጥሩ ነው " ብለዋል።

" እኛ እና እናተ ከተባበርን ሙስና ይቀንሳል፣ አገልግሎት ሊሻሻል ይችላል " ያሉት ጠ/ሚኒስትሩ " ጫካ ላሉ ሰዎች ብር ባለመላክ ብትተባበሩም እንዲሁ ይቀንሳል " ሲሉ ተናግረዋል።

" አንዳንድ በተለያየ ቦታ ሚታገሉን ሰዎች እስከ 10 ቤት በአባቱ፣ በወንድሙ  ያለው ሰው አለ፤ በረሃ ታጋይ አታጋይ የሚባል ሰው። በጣም ሃብታሞች ናቸው እዛ ተቀምጠው መነገድ የሚቻል ከሆነ ሰላም ጋር ምን አመጣቸው ሰላም ከመጣ ንግድ የለም ማለት ነው " ብለዋል።

" ቤት አላቸው፣ በተለያየ አካውንት ባንክ ውስጥ ገንዘብ አላቸው በቅርቡ እንኳን 5 ሚሊዮን ዶላር ከውጭ መጥቶ ይዘናል በአንድ #ባንክ ፣ ከፍተኛ ብር ይንቀሳቀሳል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ሃብታሞች ማወቅ ፣ መብለጥ ፣ መላቅ ስለሚመስላቸው እዚህም ይጫወታሉ እዚያም ይጫወታሉ፤ እዚህ እኛን ' የተከበራችሁ ' ይላሉ እዛ ሄደው ' እንደናተ ጀግና የለም ' ይላሉ በዚህ ሰዎቹ እየተታለሉ እንደ ስራ መስክ ይዘውት ሀገር ያምሳሉ ወጣቶች ያልቃሉ ... ችግር አለ " ብለዋል።

" እናተም ልክ የድሃ ቤት እንደምትገነቡት ሁሉ በዚህም በኩል ችግሮች እንዲፈቱ ከልባችሁ ብታግዙ ያለው ነገር ይቀንሳል " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው ምንም እንኳን ስም ባይጠቅሱም ከሀገር የወጡ ባለሃብቶች እንዳሉ ገልጸዋል።

" የሆኑ የሆኑ ሰዎች ጠፍተው ይሄዳሉ ከዚህ። ከቆየ በኃላ ስንሰማ ለምንድነው የጠፋው ሚስተር X ጥሩት ወደሀገሩ ይመለስ ሲባል ሚስተር X አይፈልግም ያደረጋቸው ትራዛክሽኖች ሁሉ ይታወቃሉ ብሎ ስለሚያስብ አይፈልግም " ብለዋል።

" እኛ እንደ መንግስት አንድም ባለሃብት ከሆነ ክልል ጋር ግጭት ስላለ ከሀገር ውጣ ያልነው የለም " ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethiopia