TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ማስታወቂያ በ2010 ዓ/ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ለወሰዳቹተማሪዎች⬇️

መቐለ ዩኒቨርስቲ፣ መቐለ የቴክኖሎጂ ኢንስቲቱዩት (MU-MIT) በተመረጡ የኢንጅነሪንግ ሳይንስና ቴክኖሎጂ የትምህርት እና የምርምር ዘርፎች የልህቀት ማእከል የመሆን ራእይ ይዞ የተቋቋመና፥ የሃገራችን የመረጃና የመገናኛ ምህንድስናና ቴክኖሎጂ የተማረ የሰው ሃይል ፍላጎት በሟሟላት የላቀ ኣስተዋጻኦ በማበርከት ላይ የሚገኝ ተቋም ነው። ኢንስቲትዩቱ ሃገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስድዉ ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች በመግቢያ ፈተና አወዳድሮ በማስገባት በሚከተሉት የትምህርት ዘርፎች በ5 ዓመት የድግሪመርሃ ግብር ያስተምራል።

📌ኬሚካል ምህንድስና (Chemical Engineering )

📌ኮምፒተር ሳይንስ እና ምህንድስና (Computer Science and Engineering )

📌ኤሌክትሮኒክስና ኮሚኒኬሽን ምህንድስና (Electronics and communication Engineering)

📌ኤሌክትሪካል ምህንድስና (Electrical Engineering)

📌ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ (Information Technology)

📌ማተርያል ሳይንስና ምህንድስና (Material Science and Engineering)

ስለሆነም በ2010 ዓ/ም ሃገር ኣቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደዉ ኢንስቲትቱ ያወጣው የመመዝገቢያ መስፈርት  ማለትም ውጤታቸዉ ከ 425 (ለወንዶች)፣ 400 (ለሴቶች) በላይ ለሆኑት በሚከተለዉ የመመዝገበያ መንገድ አንዱን በመጠቀም ከነሓሰ 09 – ጳጉሜን 02፣ 2010 ዓ/ም መመዘገብ ይችላሉ። 

በኢንስቲትቱ ድህረ ገፅ mitethiopia.edu.et. የሚል ገብታቹ Register የሚል ሊንክ በመጫን ወይም ( http://www.mitethiopia.edu.et/index.php/2018/08/11/entrance-exam-registration/#comment-1260 )

የተመዝጋቢዉ ሙሉ መረጃ ማለት
◾️ሙሉ ስም ፣
◾️የ12ኛ መመዝገበያ ቁጥር Registration ID)፣
◾️የ12ኛ ውጤትና
◾️ስልክ ቁጥር ወደ hadush@mu.edu.et ኢ-መይል በመላክ

ወደ ከታች ከተዘረዘሩትን ስልክ ቁጥሮች በመደወል

ሀ) 0345 59 4309,     
ለ) 0348 40 9872,    
ሐ) 0932 05 2216 
መ) 0911 83 2294       
ሠ) 0912 08 1941          

በኣካል ወደ ኢንስቲቱት ቴክኖሎጂ መቐለ ሬጅስትራር በመምጣት መመዝገብ ይችላሉ።

መመዝገብያ ቀን፡ ከነሓሴ 09-ጳጉሜን 02፣ 2010 ዓ/ም ብቻ!!

የፈተና ቀን፡ ቅዳሜ፣ ጳጉሜን 03, 2010 ዓ/ም

የመፈተኛ ቦታ፡ በቅርብ ቀን በሬድዮ እና በድህረ ገፅ ይነገራል.

ምንጭ:- ከ MIT ድህረ-ገፅ

©Qene Tata
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ማስታወቂያ The long awaited concert! Happening this Saturday at #Kana Studio, @Rophnan presents, MY GENERATION!

Regular tickets 250,
At the Gate 350
Tickets @VentureAddis
#ማስታወቂያ-ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ⬇️

ቀን ነሐሴ 20/2010 ዓ.ም.

የተከበራችሁ የተማሪዎች ወላጆች፦

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጅ ኢንስቲትዩት የ3ኛ ዓመት ኢንጅነሪንግ ተማሪዎች ከአጠቃላይ ፈተና (Holistic Exam ) ጋር በተያያዘ ማጠቃለያ (Final Exam) አንቀመጥም ማለታቸውን ተከትሎ የባሕር ዳር ቴከኖሎጅ ኢንስቲትዩት የአካዳሚክ ካውንስል የ3ኛ አመት ተማሪዎችን ለ1 አመት ከትምህርት ገበታ እንድታገዱ ወስኗል፡፡

ይህ ቅጣት በዩኒቨርሲቲው ሕግና በተማሪዎች መተዳደሪያ ደምብ መሰረት የመጨረሻ ትንሹ ቅጣት ነው፡፡ ሆኖም ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ወላጆች ዋና ባለድርሻ አካላት እንደሆኑ በጽኑ ያምናል፡፡ ስለሆነም በባሕር ዳርና አካባቢው ያሉ የተማሪዎች ወላጆችን አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቶ ማወያየት ስላስፈለገ በባሕር ዳርና አካባቢው የምትገኙ ወላጆች #ሰኞ ነሐሴ 21/2010 ዓ.ም. በቴክኖሎጄ ኢንስቲትዩት ፖሊ ግቢ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ በአዳራሽ ቁጥር 3 እንድትገኙ በአክብሮት ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ማስታወቂያ

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ2012 ዓ.ም. በማታ መርሃግብር ለመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት አመልካቾችን ይጋብዛል። በዚህም መሰረት አመልካቾች የሚከተሉትን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፦

1. በዲግሪያችሁ ለምታመለክቱ 40 ብር በመክፈል የወጪ መጋራት ያጠናቀቃችሁበትን የሚገልፅ ደብዳቤ ከትምህርት ማስረጃ ማቅረብ፤

2. በዲፕሎማችሁ ለምታመለክቱ150 ብር በመክፈል ከትምህርት ማስረጃ ጋር የCOC ደረጃ 3 ወይም 4 ማቅረብ

3. ዲፕሎማችሁ የአስተማሪነት ሆኖ ለምታመለክቱ 150 ብር በመክፈል ዲፕሎማ በጨረሳችሁበት የትምህርት አይነት ብቻ በመመዝገብ የትምህርት ማስረጃ ማቅረብ

4. ለPreparatory አመልካቾች ከ2004-2011ዓ.ም. ድረስ ብቻ ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መስፈርት መሰረት ለከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብን የምታሟሉ 40 ብር በመክፈል ከትምህርት ማስረጃ ጋር በማያያዝ ማቅረብ

5. ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች በተለያየ ምክንያት አቋርጣችሁ ለምታመለክቱ የወጪ መጋራት ያጠናቀቃችሁበትን የሚገልፅ ደብዳቤ 40 ብር በመክፈል ከትምህርት ማስረጃ ጋር በማያያዝ ማቅረብ

6. ለያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት እና ለአለ ፈለግ ስእል ትምህርት ቤት በቀን መርሃ ግብር ማመልከት የሚችሉት በPreparatory ከ2004-2010 ዓ.ም. ተምረው የጨረሱና ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መስፈርት መሰረት ለከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብን አምጥተው ለነበሩ የወጪ መጋራት ክፍያ ያጠናቀቁበትን ደብዳቤ ከትምህርት ማስረጃ ጋር ማያያዝ፡፡

የምዝገባ ቀን-ከነሐሴ 20 እስከ ጳጉሜ 1 2011 ዓ.ም
የምዝገባ ቦታ-በሬጅስትራር ህንፃ ቢሮ ቁጥር 203
የክፍያ ቦታ-ከሬጅስትራር ህንፃ ቢሮ ቁጥር 7 ወይም 8

ማሳሰቢያ፡-

1. አመልካቾች በዩኒቨርስቲው ድረ-ገጽ (portal.aau.edu.et ) ላይ ማመልከትና የመመዝገቢያ ቁጥሩን በመያዝ የትምህርት ማስረጃ አንድ ኮፒ ከአንድ ጉርድ ፎቶግራፍ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡

2. በዲፕሎማ አመልካቾች የዩኒቨርስቲውን የመግቢያ ፈተና ጊዜን ፤ የትምህርት ክፍሎቹን ዝርዝር እና ተጨማሪ ማብራሪያ ከዩኒቨርስቲው ድረገጽ (www.aau.edu.et) እና (www.portal.aau.edu.et) ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ያሳውቃል፡፡

#አአዩ_ሬጅስትራር

@tsegabwolde @tikvahethiopia
“ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የልጆቻችንን አእምሮ እንዲበርዙ መፍቀድ የለብንም ” - ስፔንሰር ኮክስ

የአሜሪካ ሀገር " ዩታህ ግዛት " በታዳጊዎች ፌስቡክ፣ ቲክቶክ እና ኢነስታግራምን የመሰሉ ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማቸው ላይ ገደብ ጣለች።

ይህ በማድረግ አሜሪካ ውስጥ የመጀመሪያዋ ግዛት ሆናለች።

ትላንት ሀሙስ በፀደቀው ደንብ መሰረት ወላጅ ወይም አሳዳጊ ልጆቹ #ኢኒስታግራም#ፌስቡክ እና #ቲክቶክ ከመክፈቱ በፊት የወላጅ ይሁንታ ማግኘት ይኖርበታል።

የፀደቀው ደንብ ምን ይዟል ?

- የማኅበራዊ ሚዲያ አገልግሎት አቅራቢ ኩባንያዎች ለልጆች አገልግሎቱን ከማቅረባቸው በፊት #የወላጆችን ይሁንታ ማግኘት ይኖርባቸዋል።

- ወላጅ ወይም አሳዳጊ ልጆቹ #ኢኒስታግራም#ፌስቡክ እና #ቲክቶክ ከመክፈቱ በፊት የወላጅ ይሁንታ ማግኘት ይኖርበታል።

- ኩባንያዎች መተግበሪያዎቻቸው ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ አዳጊዎች ያለ ወላጅ ይሁንታ እንዳይከፍቱ ያደረጋሉ።

- ኩባንያዎቹ የአዳጊዎቹን የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም፣ ታሪክ፣ የለጠፏቸውን እና በግል #የተጻጻፏቸውን_መልዕክቶች ሁሉ ለወላጆች መስጠት ይገደዳሉ።

- የማኅበራዊ ሚዲያ አቅራቢ ኩባንያዎች የልጆቹን ፍላጎት እና ምርጫ መሠረት አድርገው #ማስታወቂያ በልጆቹ የማኅበራዊ ሚዲያ ሰሌዳቸው ላይ እንዳይለቁ ይገደዳሉ።

- ታዳጊዎች ማኅበራዊ ትስስር መድረኮችን ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት እስከ ንጋት 12፡30 ድረስ መጠቀም እንዳይችሉ ይደነግጋል።

ሕጉ ተግባራዊ መሆን የሚጀምረው ከሚቀጥለው ዓመት መጋቢት ጀምሮ ነው።

ይህን እርምጃ መውሰድ ያስፈለገው ማኅበራዊ የትስስር መድረኮች በልጆች #የአእምሮ_ጤና ላይ ከፍ ያለ መረበሽን እያደረሱ መሆኑ ከተደረሰበት በኋላ ነው ተብሏል።

የዩታህ ግዛት ገዢ ስፔንሰር ኮክስ በትዊተር ገፃቸው ላይ ፤ “ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የልጆቻችንን አእምሮ እንዲበርዙ መፍቀድ የለብንም ” ሲሉ ጽፈዋል።

ከዩታህ በተጨማሪ ተመሳሳይ ሕጎች በቴክሳስ፣ በኦሃዮ፣ በአርካንሳስ፣ በኒው ጀርሲ እና በሊዊዚያና ግዛቶች እየተረቀቁ ነው መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል።

Credit : #BBC

@tikvahethiopia