TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ይህችን እስራኤላዊ ያለችበትን የሚያውቅ በዚህ ስልክ ቁጥር ደውሎ ያሳውቀን +251 - 914940462

Dear Ethiopia.

I write you with urgent news. One of my town residents was on a trip to Ethiopia and went missing.

She was last seen hiking in the Danakil depression area and went missing after. She is 22. My entire town is nervous for her - and I hope you can help us share this message around to find her.

Thank you so much Ethiopia.
If you have any information on her, please call: +251 - 914940462

#NAS_DAILY

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በ2012 ዓ.ም በዩኒቨሲርቲዎች፦

• ለመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች 15 አዳዲስ ትምህርቶች ይሰጣሉ
• የዲግሪ ፕሮግራም አራት ዓመት ይሆናል

በ2012 ዓ.ም ወደ መንግሥትም ሆነ የግል ዩኒቨርሲቲዎች የሚገቡ አዲስ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች ትምህርት የሚጀምሩት በ15 አዳዲስ ትምህርቶች መሆኑን የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አስታወቀ። በሦስት ዓመታት ይጠናቀቅ የነበረው የዲግሪ ፕሮግራም ወደ አራት ዓመት ከፍ ብሏል።

ዩኒቨርሲቲዎቹ በ2012 ዓ.ም ለመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች የሚሰጡት ክሪቲካል ቲንኪንግ፣ ሂስትሪ(ታሪክ) ኤንድ ዘሆርን፣ ጂኦግራፊ ኤንድ ዘሆርን፣ አንትሮፖሎጂ፣ ሳይኮሎጂ፣ ሂሳብ እና ሌሎቹም ለሁሉም የሚሰጡ የጋራ (ኮመን ኮርሶች ) ሲሆኑ ይህም ተማሪዎች በአስተሳሰብ ምጡቅ እንዲሆኑ፣ ብዝሀነትን፣ የሀገርን ባህል፣ አገር በቀል ዕውቀቶችንና ታሪክ እንዲያውቁ የሚያደርጉ ናቸው።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አንዱአለም አድማሴ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ጥራት፣ ስነምግባር እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በሚመለከት የሀገሪቱ የትምህርት ስርዓት እንዴት ይቃኝ በሚለው ላይ ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ በምሁራን ሰፊ ጥናት ሲደረግና በርካታ ህዝብም ሲወያይበት ቆይቷል። ይሄንኑ መነሻ በማድረግም ብዙ ማሻሻያ እና ለውጦች ተደርገዋል።

በዚሁ መሰረት በ2012 ዓ.ም #ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለሚገቡ ተማሪዎች አዳዲስ ኮርሶችን መስጠት እንዲችሉ ስምምነት ላይ ተደርሶ ለዚሁ ዝግጅት መደረጉን ጠቅሰው፣ አሁን ያለው ሁኔታ ትምህርቱን ለመጀመር የሚቻል ነው ብለዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ET-08-18

Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በ2012 ዓ.ም ለመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች የሚሰጡት የትምህር ዓይነቶች ለሁሉም የትምህርት ክፍሎች የጋራ እንደሚሆኑ ታውቋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እስራኤላዊቷ ተማሪ ህይወቷ አልፏል!!

የ21 አመቷ እስራኤላዊት #አያ_ናምኔህ ህይወት አልፎ መገኘቷን #TheJerusalemPost ከደቂቃዎች በፊት ዘግቧል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የእስራኤላዊቷን ተማሪ አስክሬን የያዘው ሂሊኮፕተር🚁ወደ አዲስ አበባ እየተመለሰ ነው! #ESK #ETHIOPIA #ET

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከደብረ ብርሃን...

"በደብረ ብረሀን አካባቢ በሚገኘው የሚኒሊክ የትውልድ ስፍራ አንጎለላ #እንቁላል_ኮሶ የሚኒሊክ 175ኛ አመት የልደት በዓል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል" ሠለሞን ከበደ ከደብረ ብርሃን

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በቦንብ ጥቃት የ63 ሰዎች ማለፉ ተሰማ!

በአፍጋኒስታን መዲና ካቡል ከተማ የሰርግ ስነ ስርዓት ላይ በተፈጸመ የቦምብ ጥቃት የ63 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡ በጥቃቱ ህይወታቸው ካለፈው 63 ሰዎች በተጨማሪ ከ180 በላይ የሰርጉ ታዳሚዎች መቁሰላቸው ተነግሯል፡፡

ጥቃቱ በአጥፍቶ ጠፊዎች ስለመፈጸሙ የአይን እማኞች ለመገናኝ ብዙሃን ተናግረዋል፡፡ ጥቃቱ የተፈጸመው በመዲናዋ ምዕራባዊ ክፍል የሺዒኣ ሙስሊሞች በብዛት በሚኖሩበት አካባቢ ነው ተብሏል፡፡ የታሊባን ተዋጊዎች ቡድን ከዚህ ጥቃት ጀርባ እንደሌለበት አስታውቋል፡፡ እስካሁን የጥቃሩን ሃለፊነት የወሰደ አካል እንደሌለም ነው ዘገባው የሚያስረዳው።

ምንጭ፡- ቢ ቢ ሲ/fbc
ፎቶ: VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኦሮሚያ ክልል የተለያዩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የተሳተፉበት የፅዳት ዘመቻ ዛሬ በአዲስ አበባ ኦሮሞ ባህል ማእከልና አካባቢው ተካሂዷል። በመላው ኢትዮጵያ በዛሬው እለት አገር አቀፍ የፅዳት ዘመቻ በመካሄድ ላይ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዓብይ አህመድም ዛሬ ማለዳ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ኢተያ ከተማ በተካሄደው የፅዳት ዘመቻ ላይ ተሳትፈዋል።

በአዲስ አበባም የከተማው ነዋሪዎች፣ የመንግስት ባለስልጣናትና የተለያዩ ድርጅቶች ዛሬ ከማለዳው  ጀምረው አካባቢያቸውን በማፅዳት ላይ ናቸው። በከተማዋ በሚገኘው የኦሮሞ ባህል ማዕከልና አካባቢው ላይም በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ቢሮ  ኃላፊዎችና ሰራተኞች ተሳትፎ የፅዳት ዘመቻው ተካሂዷል።  በአካባቢው የችግኝ ተከላም አከናውኗል። የጽዳት ዘመቻው በሁሉም የኦሮሚያ ክልል በመካሄድ ላይ መሆኑም ታውቋል።

Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢ/ር ታከለ ኡማ በከተማዋ ባሉ የተለያዩ ትምህርት ቤቶች በመገኘት የዕድሳት ሂደቱ ያለበትን ደረጃ ተመልክተዋል፡፡ ቦሌ መሠናዶ ፣ ኮከበ ጽበሃ እና ጥቁር አንበሳ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በዛሬው ዕለት ምልከታ ከተደረገባቸው ትምህርት ቤቶች ውስጥ ይገኙበታል፡፡

Via MayorOfficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢንሳ የቀድሞ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሌተናል ኮሎኔል ቢኒያም ተወልደ ዋስትና ታገደ!

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ሐምሌ 29 ቀን 2011 ዓ.ም. በ30,000 ብር ዋስ ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ የሰጠ ቢሆንም፣ ከሳሽ ዓቃቤ ሕግ ለይግባኝ ሰሚው ችሎት ይግባኝ አቅርቦ እንዲታገድ አድርጓል፡፡

በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው #በእስር ላይ የሚገኙት ቀድሞ የኢትዮጵያ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ (ኢንሳ) ምክትል ዳይሬክተር ሌተና ኮሎኔል ቢኒያም ተወልደ፣ በተመሠረተባቸው ክስ እንዲከላከሉ ብይን ተሰጥቶባቸው ነበር፡፡ የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007፣ አዋጅ ቁጥር 780/2005፣ አዋጅ ቁጥር 591/2007 የወንጀል ሕግ 808 ተላልፈዋል በማለት ዓቃቤ ሕግ እንደ ክሱ በማስረዳቱ በአምስት ክሶች  እንዲከላከሉ ብይን ተሰጥቶ ነበር፡፡

የተጠቀሱባቸው #የሕግ ድንጋጌዎች #ዋስትና እንደማይከለክሉ በማስረዳት ሌተና ኮሎኔል ቢኒያም በጠበቃቸው አማካይነት ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸውን እንዲጠብቅላቸው ጠይቀው ነበር፡፡ ዓቃቤ ሕግ በተከሳሹ ላይ የተጠቀሱት ሕጎች ከ15 ዓመታት በላይ ሊያስቀጧቸው እንደሚችሉ በመግለጽ፣ የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ እንዲደረግ ተከራክሮ ነበር፡፡

ፍርድ ቤቱ የዋስትና ጥያቄው የሕግ ክልከላ ያለበት ነው ወይስ አይደለም የሚለውን መርምሮ፣ የዓቃቤ ሕግን መቃወሚያ ውድቅ በማድረግ በ30,000 ብር ዋስትና እንዲለቀቁና ዓቃቤ ሕግ ይግባኝ የሚል ከሆነ በማለት አሥር ቀናት ለመጠባበቂያ ሰጥቶ ነበር፡፡ ዓቃቤ ሕግም ይግባኙን ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት አቅርቦ ‹‹ያስቀርባል›› በመባሉ፣ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ትዕዛዝ እስከሚሰጥ ዋስትናው መታገዱ ታውቋል፡፡

Via Reporter
@tsegabwolde @tikvahethiop
#ነቀምቴ አንድነታቸውን አጠናክረው ለአካባቢያቸው ጽዳትና ደህንነት ተግተው እንደሚሰሩ በነቀምቴ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። ብሔራዊ የጽዳት ቀን ዛሬ በነቀምቴና ቁኒ ከተሞች ተካሄዷል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እሁድ እንዴት እያለፈ ነው?

የለኩ ወጣቶች ቀኑን በበጎ ስራ እያሳለፉት እንደሚገኙ ነግረውናል፦

*የለኩ እኔም ለወገኔ የበጎ አድራጎት ማህበር በከተማውና በሸበዲኖ ወረዳ ከሚገኙ 12 ቀበሌዎች ላይ ያሉ እጅግ የተቸገሩ 60 አረጋዊያንን እና ከ 200-500 ሚደርሱ ተማሪዎችን በመርዳት ላይ የሚገኝ ማህበር ሲሆን ለ 2012 ከህዝብ ከሚሠበሠብ ገንዘብ በተጨማሪ የተለያዩ ገቢ ማስገኛዎችን በመንደፍ በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል ዛሬም ቡና ና ሊስትሮ በመጥረግ ላይ እንገኛለን። ስለሆየም ሁላችንም ከተረፈን ሳይሆን ካለን ነገሮች ላይ በማካፈል ከጎናችን እንድትቆሙልን ስንል በትህትና እንጠይቃለን!"

0939467113
0916336699
0985099944

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እሁድ እንዴት እያለፈ ነው?

የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ቀኑን ለወገናቸው ደም በመለገስ እያሳለፉ ይገኛሉ። ሶስት ቁጥር ማዞርያ ቶታል አካባቢ የሚገኙ ደጋፊዎች!

"ስንደመር ያምርብናል፤ በደማችን ሰው ይድናል"

ፎቶ📸Buna Gebya
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እሁድ እንዴት እያለፈ ነው?

#ባይሽ_ኮልፌ

"እኛ ደግሞ ለ18 አመታት ጫካ ውስጥ ትኖር የነበረችውን እናት የቀበሌ ቤት ተሰጥቷ አድሰንላት ቤት አስገብተናት አብረናት እያሳለፍን ነው"

"ከእንግዲህ ብሞትም አይቆጨኝም!" እማማ አስቴር መንግስቱ

እናታችን ወደ ቤታቸው ሲገቡ በደስታ አልቅሰዋል! በሆነዉ ሁሉ ተገርመዋል። እንዲህም አሉን"ልጄ ዉሀ ላይ እየተኛ ሞራሉ ተነክቶአል። ትምህርቱን እንኳን እንደ #ጏደኞቹ ጠንክሮ #መማር አልቻለም አሁን ግን ቤት አለዉ #ብሞትም አይቆጨኝም። እኛን እንዳስደሰታችሁ ፈጣሪ እናንተን ያስደስትልኝ!" ከዚህ በላይ ደስታ የት አለ? "ኑ ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም!!!"

#ባይሽ_ኮልፌ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እሁድ እንዴት እያለፈ ነው?

በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ የሚገኙ ወጣቶች እና የከተማ ነዋሪዎች እሁድን ለወገኖቻቸው ደም በመለገስ እያሳለፉ እንደሚገኙ ነግረውናል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሓደ ጥማር ንሓደ ህፃን
አንድ እሽግ ለአንድ ህፃን
One Pack For One Child


ኮኸብ ፅባሕ መተሐጋገዝን መረዳድእን ሰገናት ማሕበር - #መቐለ, #ትግራይ

📞0914271942
📞0914708858

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ወጣቶች የስደትን መራራነት ተረድተው ከስደት መታቀብ አለባቸው"–በሱዳን ተመላሽ ስደተኞች #ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት እሌኒ መ/መ/ሆስፒታል ድንገተኛ ጉብኝት አደረጉ!

የኢፌዴሪ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ ከሌሎች የፌዴራል እና የዞን አመራሮች ጋር በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ስር የሚገኘውን የንግስት እሌኒ መ/መ/ሆስፒታል ድንገተኛ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በጉብኝቱ ወቅት ዶ/ር ሐብታሙ አበበ የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት እና ዶ/ር አያኖ ሻንቆ በም/ፕሬዝዳንት ማዕረግ የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር እየተጠናቀቁ ያሉ ግንባታዎች ላይ ለድንገቴ ክቡራን እና ክቡራት ጎብኝዎች ገለፃ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ማህበረሰብ ተስፋ ሲቆርጥ ምን ይፈጠራል?

"...እንደ ህዝብ ደግሞ ህዝብ ተስፋ ከቆረጠ እሴቶቹን ይጥላል፤ ነገ ለውጥ የለም፤ ምንም ተስፋ የለንም ብሎ ካሰበ፤ ይጋደላል፣ ይሰዳደባል፣ ተስፋ የቆረጠ ሰራዊት ልታይ ትችላለህ ፌስቡክም ላይ ሚዲያም ላይ፤ ህዝብ ተስፋ ከቆረጠ መከባበሩ ይጠፋል፤ ትህትናው ይጠፋል፤ ፍቅሩ ይጠፋል፤ ሚታየው ነገር የለም። ሰውን ስነ ስርዓት ከሚያሲዙትና እሴቶቹን ጠብቆ እንዲኖር ከሚያደርጉት ነገሮች አንዱ ነገ መልካም ይሆናል የሚል #ተስፋ ነው" ዶክተር #ወዳጄነህ_ማሀረነ

#HOPE #TIKVAH/#ተስፋ/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeTelegramChannel ይህ "ልዩ መረጃ ከኤልያስ ጋር" የሚለው ገፅ ሀሰተኛ ነው። ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት "ልዩ መረጃ" በሚል ምንም አይነት የፌስቡክ ገፅም ሆነ የቴሌግራም ቻናል እንደሌለኝ እወቁልኝ ብሏል። ለቴሌግራም Report እንድታደርጉም ጥሪ እናቀርባለን።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር!

የተማሪዎችን ብቃት፣ ክህሎትና ተግባቦት በማጠናከር አጠቃላይ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ያስችላሉ ተብሎ የታመነባቸው አዳዲስ የትምህርት ዓይነቶች (ኮርሶች) በሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ከመጪው ዓመት ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በዚህም መሰረት ቀደም ሲል በሶሰት ዓመት ይጠናቀቅ የነበረው የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ትምህርት መርሃ ግብር ወደ አራት ዓመት ከፍ እንዲል ይደረጋል ተብሏል።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-08-18

@tsegabwolde @tikvahethiopia