የኦሮሚያ ክልል የተለያዩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የተሳተፉበት የፅዳት ዘመቻ ዛሬ በአዲስ አበባ ኦሮሞ ባህል ማእከልና አካባቢው ተካሂዷል። በመላው ኢትዮጵያ በዛሬው እለት አገር አቀፍ የፅዳት ዘመቻ በመካሄድ ላይ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዓብይ አህመድም ዛሬ ማለዳ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ኢተያ ከተማ በተካሄደው የፅዳት ዘመቻ ላይ ተሳትፈዋል።

በአዲስ አበባም የከተማው ነዋሪዎች፣ የመንግስት ባለስልጣናትና የተለያዩ ድርጅቶች ዛሬ ከማለዳው  ጀምረው አካባቢያቸውን በማፅዳት ላይ ናቸው። በከተማዋ በሚገኘው የኦሮሞ ባህል ማዕከልና አካባቢው ላይም በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ቢሮ  ኃላፊዎችና ሰራተኞች ተሳትፎ የፅዳት ዘመቻው ተካሂዷል።  በአካባቢው የችግኝ ተከላም አከናውኗል። የጽዳት ዘመቻው በሁሉም የኦሮሚያ ክልል በመካሄድ ላይ መሆኑም ታውቋል።

Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia