TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጀግኒት #ከጅማ_ዞን #ጌራ_ወረዳ

"እቅዴ ከዚህም በላይ ነበር፤...ይህን በማምጣቴ ደስ ብሎኛል"

"የአፕቲትዩድ ውጤቴ መጀመሪያ 29 ነበር፤...ተስተካክሎ የመጣው 97 ነው"

"የመጀመሪያ ፈተና ስለነበር ደንግጬ ነበር ፈርቼም ነበር፤ ...ወደ መልስ መስጫ ወረቀቴ በችኮላ ነው የገለበጥኩት በዛ ሰዓት የፈጠርኩት ስህተት ነው ብዬ ገምታለሁ"

"ያለኝን ሰዓት በሙሉ ነበር ተጠቅሜ እያነበብኩ የነበረው"

"የስልክ ተጠቃሚ አይደለሁም፤ የማህበራዊ ሚዲያም ላይ የለሁም፤ ያለኝን ሰዓት በሙሉ ማሳለፍ የምፈልገው በትምህርቴ ላይ ብቻ ነው"

"በራሴ ስለምተማመን ሜዲስን እደምገባ እርግጠኛ ነኝ፤ እዛም ሰቅዬ እንደምወጣ እርግጠኛ ነኝ!"

"ከ1ኛ ክፍል ጀምሮ እስካሁን 1ኛ ነው የወጣሁት"

"ለዚህ ፈተና መዘጋጀት የጀመርኩት ከ11ኛ ክፍል ጀምሮ ነው።"

#ነኺማ_ቲጃኒ በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን #ጌራ_ወረዳ በሚገኘው የጌራ ፕሪፓራቶሪ ትምህርት ቤት ተማሪ ናት በዘንድሮው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና 638 ነው ያስመዘገበችው። TIKVAH-ETH ከታች ላሉት ተማሪዎች ተሞክሮዋ ይጠቅማል ብሎ በማሰብ አነጋግሯታል በቀጣይ ቀናት ይቀርባል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia