TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Professor

11 ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ተሰጣቸው።

አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ11 ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል።

በዩኒቨርሲቲ የውስጥና ውጭ ገምጋሚዎች በጥልቀት ተመርመሮ ፣ በኮሌጆች የአካዳሚክ ኮሚሽኖች ተፈትሾ ፣ በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ታይቶና ይሁንታ አግኝቶ የቀረበለትን መረጃ ከተመለከተ በኋላ የየኒቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ ለ11 ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል።

የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው፦

1. ዶ/ር ቁምላቸው የሺጥላ፣  
2. ዶ/ር ሽመልስ አሰፋ፣  
3. ዶ/ር መንግስቱ ለገሰ፣
4. ዶ/ር ጉታ ዘነበ፣
5. ዶ/ር ፋሲል አሰፋ፣  
6. ዶ/ር ጥልዬ ፈይሳ፣
7. ዶ/ር ብሩክ ላምቢሶ፣  
8. ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ አለሙ፣  
9. ዶ/ር ዘበነ ክፍሌ፣  
10. ዶ/ር ተረፈ ደገፋ እና
11. ዶ/ር ንጉሴ ደየሳ መሆናቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ምሁራኑ የ #ሙሉ_ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው
በመማር ማስተማር፣ በጥናትና ምርምር እንዲሁም በማኅበረሰብ ዐቀፍ እና ሙያዊ አገልግሎት የነበራቸው አበርክቶ ተገምግሞ መሆኑ ታውቋል።

@tikvahuniversity @tikvahethiopia