TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
app.neaea.gov.et

የተስተካከለውን የአፕቲትዩድ ውጤት ከዛሬ ምሽት ጀምሮ መመልከት እደምትችሉ የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታውቋል።

ተማሪዎች ውጤታችሁን በሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ድረ-ገጽ app.neaea.gov.et በመግባት Admission በሚለው ሳጥን ውስጥ የመፈተኛ ቁጥራቸውን (Registration Number) በማስገባትና go የሚለውን አንዴ click በማድረግ መመልከት ትችላላችሁ።

#ሼር #share

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለአዲስ አበባ መምህራን ታብሌት ሊሰጥ ነው!

በአዲስ አበባ ለሚገኙ መምህራን የትምህርት ዝግጅትና ቁጥጥር የሚያደርጉበት እንዲሁም የትምህርት እቅድ የሚያወጡበት ታብሌት ሊሰጥ ነው። የከተማ አስተዳደሩ በአዲስ አበባ ያለውን የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ በከፍተኛ ደረጃ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል፡፡

በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን በከተማዋ ለሚገኙ የመንግስት ት/ቤት መምህራን የትምህርት ዝግጅት እና የትምህርት እቅድ የሚያወጡበት ታብሌት ለመስጠት የከተማ አስተዳደሩ ዝግጅቱን አጠናቅቋል፡፡ ለዚህ የሚረዱ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑም ይገኛሉ።

ታብሌቶቹ በሳተላይት የሚገናኙ ሲሆን መረጃዎችን ወደ ማእከል የሚልኩበት መተግበሪያዎችን ያካተተም ይሆናል። ከታብሌቶቹ በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ ዓርማ ያረፈበት ቦርሳ እና ደረጃውን የጠበቀ ገዋን ለመምህራን የሚያቀርብ ይሆናል።

በመምህራን የሚነሱ የተለያዩ ጥያቄዎችን ለመመለስም የከተማ አስተዳደሩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራም ይገኛል። በቀጣይ አመት ለመምህራን ቁሳቁሶች የማሟላቱ ተግባር የከተማ አስተዳደሩ በአዲሱ አመት በከተማዋ ለሚገኙ 600ሺ የመንግስት ት/ቤት ተማሪዎች ዩኒፎርምና የመማሪያ ቁሳቁሶች የማቅረብ ፕሮጀክት አካል ነው።

Via MayorOfficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አፕቲትዩድ

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ከስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ዉጪ በሌሎች የትምህርት አይነቶች የፈተና አስተራረም ችግር አለመፈጠሩ ተገለጸ።

የሃገር አቀፍ ፈተናና ምዘና ኤጀንሲ ተማሪዎች ቅሬታ ሲቀርብበት የነበረውን የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና የስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ውጤትን መመልከት እንደሚችሉ አስታውቋል።

ኤጀንሲው ከፈተናው የመልስ ቁልፍ ጋር ተያይዞ የነበረው እርማት ተጠናቆ በድረ ገጹ እና በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መመልከት ይችላሉ ብሏል። የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዓርዓያ ገብረእግዚአብሄር እንዳሉት የስኮላስቲክ ፈተናው ኮድ 21 እና 22 ችግር እንደነበረባቸው ጠቅሰዋል።

ዳይሬክተሩ ቀደም ሲል በአጭር የፅሁፍ መልዕክት እና በድረ ገጽ መለቀቁን ጠቅሰው፥ የተለቀቀው ውጤት ያልተስተካከለው እንደነበር ገልጸዋል። ለዚህም ቀደም ሲል በአጭር የፅሁፍ መልዕክት የተለቀቀውን መረጃ ማጥፋት የሌላ አካል ሃላፊነት መሆኑንም አንስተዋል፡፡

ከፈተናው ጋር ተያይዞ ለኤጀንሲው 10ሺህ ያህል ቅሬታዎች መቅረባቸውን ያነሱት ዳይሬክተሩ፥ አሁን ላይም ጉዳዩን የሚከታተል ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ይሁን እንጅ እስካሁን በሌሎች የትምህርት አይነቶች ችግሮች ያለመገኘታቸውን አስረድተዋል። የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት እርማት ሃምሌ 20 ቀን 2011 መጠናቀቁን የተናገሩት ዳይሬክተሩ ፈተናው ይፋ እስከሚደረግ ድረስ ባሉት ጊዜያትም መሰል ችግሮች እንዳይከሰቱ የማጣራት ስራ ሲሰራ እንደነበረም አስታውሰዋል፡፡

Via #ETHIOFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"...ከንቱ ድካም ነው። በሌሎች ትምህርቶች ላይ የተስተዋለ ችግር የለም።" አቶ #አርዓያ

በሁሉም ትምህርቶች ውጤት ላይ እየቀረበ ያለው ቅሬታ ተገቢ ያልሆነ በመሆኑ ተቀባይነት የለውም ሲሉ አቶ አርዓያ ገ/እግዚያብሄር ለጀርመን ራድዮ ተናገሩ። “አሁን ተማሪዎች በአካል እየመጡም ይሁን በድረ ገጽ እያቀረቡት ያለው ቅሬታ ኤጀንሲው ችግር አለበት ካለው አይነት በላይ በመሆኑ ቅሬታ ማቅረባቸው ትርጉም አይኖረውም ማለት ነው ወይ?” ተብለው የተጠየቁት አቶ አርአያ “አዎ! ከንቱ ድካም ነው። በሌሎች ትምህርቶች ላይ የተስተዋለ ችግር የለም። የሚስተካከልም ነገር አይኖርም” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በዩኒቨርሲቲ መግቢያ የፈተና ውጤት ላይ የቀረቡ ቅሬታዎች!

የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ይፋ ያደረገው የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ቅሬታ ማስነሳቱን ተከትሎ ኤጀንሲው ካለፈው ሰኞ ጀምሮ የቅሬታ መቀበያ ቅጽ በመስጠት ቅሬታዎችን እየተቀበለ ይገኛል።

በኤጀንሲው ዋና መስሪያ ቤት በአካል መገኘት ቅሬታቸውን ሲያቀርቡ ያገኘናቸው ተማሪዎች ውጤቱ ዳግም እንዲመረመር ጠይቀዋል። ከተለያየ የሃገሪቱ አካባቢዎች የመጡት ወላጆች “የተጠበቀው ቀርቶ ያልተጠበቀው መከሰቱ እንዳሳዘናቸው” ገልጸዋል። መንግስት ትውልድ የደከመበትን ይህንን ጉዳይ በጥሞና እንዲያጤነውም ጠይቀዋል።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ አርአያ ግብረእግዚአብሄር ችግር የተስተዋለበት የስኮላስቲክ አፕቲትዩድ የትምህርት አይነት ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም የፈተና ኮድ 21 እና 22 ላይ ብቻ የተከሰተ በመሆኑ እንደገና ታይቶ እና ታርሞ መጠናቀቁን ገልጸዋል። አዲሱ ውጤት ዛሬ አልያም ነገ ይፋ እንደሚደረግ የጠቆሙት ዋና ዳይሬክተሩ ይህን ተከትሎም “ቢያንስ ከተፈታኞች መካከል በግማሽ ያህሉ የተማሪዎች ውጤት ላይ ለውጥ ይኖራል” ብለዋል።

ይሁንና በሁሉም ትምህርቶች ውጤት ላይ እየቀረበ ያለው ቅሬታ ተገቢ ያልሆነ በመሆኑ ተቀባይነት የለውም ብለዋል። “አሁን ተማሪዎች በአካል እየመጡም ይሁን በድረ ገጽ እያቀረቡት ያለው ቅሬታ ኤጀንሲው ችግር አለበት ካለው አይነት በላይ በመሆኑ ቅሬታ ማቅረባቸው ትርጉም አይኖረውም ማለት ነው ወይ?” ተብለው የተጠየቁት አቶ አርአያ “አዎ! ከንቱ ድካም ነው። በሌሎች ትምህርቶች ላይ የተስተዋለ ችግር የለም። የሚስተካከልም ነገር አይኖርም” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

Via #DW

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የመልሶ ማሰተካከያው ዕርማት በ148,734 ተማሪዎች ውጤት ላይ በማደግ ለውጥ አምጥቷል!

ለ12ተኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ!

የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ /የ12ኛ ክፍል/ ፈተና ውጤት ከስኮላስቲክ አፕቲቲዩድ የፈተና ውጤት ጋር በተያያዘ ከተማሪዎች፣ ከወላጆች እና ከመምህራን ስፋት ያለው ቅሬታ በመቅረቡ አገር- አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች ኤጄንሲ ጉዳዩን በማጣራት ባደረገው የመልሶ ማሰተካከያ ዕርማት የ148,734 ተማሪዎች ውጤት ላይ በማደግ ለውጥ ያመጣ ሥለሆነ ዝርዝር ውጤታችሁን በአገር-አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች ኤጄንሲ ዌብ-ሳይት ላይ በሚቀጥሉት ቀናት እንድትመለከቱ ትምህርት ሚኒሰቴር ያስታውቃል፡፡

ትምህርት ሚኒሰቴር
Ministry of Education Ethiopia


@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፓስፖርት መስጠት ተጀመረ!

ፓስፖርት ለመስጠት የድጋፍ ደብዳቤ መጠየቅን በማቆም በመታወቂያ እና ልደት ሰርተፊኬት ፓስፖርት መስጠት መጀመሩን የኢሜግሬሽን፣ ዜግነት እና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ ኤጀንሲው ከመጪው ሰኞ ጀምሮ ፓስፖርት ለመውሰድ ጥያቄ የሚያቀርቡ አካላት ህጋዊ መታወቂያ እና የልደት ሰርተፊኬት ማቅረብ አለባቸው ብሏል፡፡

 Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አቶ አርዓያ ከetv ጋር ያደረጉት ቆይታ!

ተማሪዎች #የተስተካከለውን የ12ኛ ክፍል የስኮላስቲክ አፕቲትዩድ ፈተና ውጤት ከዛሬ ጀምሮ መመልከት እንደሚችሉ የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታውቋል።

Vid.10MB
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የተስተካከለው ውጤት ይፋ ሆኗል!

app.neaea.gov.et

የተስተካከለውን የአፕቲትዩድ ውጤት #ከዛሬ ጀምሮ መመልከት እደምትችሉ የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታውቋል።

ተማሪዎች ውጤታችሁን በሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ድረ-ገጽ app.neaea.gov.et በመግባት Admission በሚለው ሳጥን ውስጥ የመፈተኛ ቁጥራቸውን (Registration Number) በማስገባትና go የሚለውን አንዴ click በማድረግ መመልከት ትችላላችሁ።

#ሼር #share

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በግለሰብ ደረጃ የቀረቡ ሁሉም አቤቱታዎች እየተጣሩ እንደተለመደው መልስ የሚሠጥ መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን!"

ለተከበራችሁ የ2011 የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች!

የ2011 የፈተና ውጤት መለቀቅን ተከትሎ ከውጤቱ ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ማቅረባችሁ ይታወሳል። በዚሁ መሠረት ኤጄንሲው ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት ሠጥቶ ባደረገው ማጣራት የስኮላስቲክስ አፕቲቲዩድ ትምህርት ኮድ 21 እና 22 የመልስ መፍቻ “Answer Key” ለማረሚያ ማሽን ሲሠጥ መቀያየር እንደነበረ ማረጋገጥ ተችሏል። በዚህ መሠረት በትክክለኛው የመልስ መፍቻ መሠረት ታርሞ የተስተካከለው ውጤት ለተማሪዎች ተለቋል። በአዲሱ ውጤት መሠረት በኮድ 21 እና 22 ከተፈተኑ ተማሪዎች መካከል የ148,734 ተማሪዎች ውጤት በማዳግ ለውጥ አሳይቶዋል። ስለሆነም ተማሪዎች ውጤቱን በተለመደው መንገድ ኦንላይን ገብተው ማየት የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን። (ውጤታችሁን በSMS የምታዩ ተማሪዎች አዲሱ ውጤት በነገው ቀን የሚጫን ይሆናል)

በሌሎች የትምህርት ዓይነቶች ላይ የቀረቡ አቤቱታዎች በተመለከት በተቀሩ የትምህርት ዓይነቶች ላይ የመልስ ቁልፍ ችግር አለማጋጠሙ ተረጋግጧል። ነገር ግን በግለሰብ ደረጃ የቀረቡ ሁሉም አቤቱታዎች እየተጣሩ እንደተለመደው መልስ የሚሠጥ መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን።

የሀገር አቀፍ ትምርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጀግኒት

ተማሪ NEIMA TIJANI ABABIYA በዘንድሮው የዩኒቨርሲቲ /የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ/ ፈተና 638 ያስመዘገበች ኢትዮጵያዊት ናት! TIKVAH-ETH በቀጣይ ቀናት አስተያየቷን ይዞ ለመቅረብ ጥረት ያደርጋል። #Jimma #GERA #638

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጀግኒት

ተማሪ ቃልኪዳን አስቻለው በዘንድሮው የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና 643 ያስመዘገበች ኢትዮጵያዊት ናት! TIKVAH-ETH በቀጣይ ቀናት አስተያየቷን ይዞ ለመቅረብ ጥረት ያደርጋል። #643 #አዲስአበባ #ካቴድራል

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጀግኒት

ተማሪ SANNE KEFYALEW ROBA በዘንድሮው የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና 606 ያስመዘገበች ጀግኒት! #ኢትዮጵያዊት!

#606 #ዲላ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጀግኒት

ተማሪ SELAMAWIT TEKLAY በዘንድሮው የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና 618 ያስመዘገበች ጀግኒት! #ኢትዮጵያዊት

#618 #ጎንደር #ፋሲለደስ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጀግኒት

ተማሪ BONTU BENTI በዘንድሮው የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና 610 ያስመዘገበች ጀግኒት! #ኢትዮጵያዊት

#610 #አዳማ #ODA_SPECIAL_BOARDING

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጀግኒት

ተማሪ SELAMAWIT KASSAHUN #በዘንድሮው የዩኒቨርሲቲ/የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና 616 ያስመዘገበች ጀግኒት! #ኢትዮጵያዊት

#616 #ቢሾፍቱ

🗓የሌሎች #ጀግኒቶች ውጤት ይቀጥላል🔄
#ካርቱም

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶክተር) የሚመሩት ልዑክ ካርቱም ገብቷል፡፡ በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በማኅበራዊ ገጹ እንዳስነበበው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩት ልዑክ ዛሬ ወደ ሱዳን ያቀናው በሱዳን የሽግግር መንግሥትን በይፋ ለመመሥረት በሚከናወነው ሥነ-ሥርዓት ለመታደም ነው፡፡

የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሐሰን ኦማር አልበሽር መንግሥት የሦስት አስርት ዓመታት ቆይታው በሕዝባዊ ተቃውሞ ተናግቶ ወታደራዊ የሽግግር ምክር ቤት ሲመሠረት ሱዳን ወደ ቀውስ እንደምትገባ ብዙዎች ገምተው ነበር፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያና የአፍሪካ ሕብረት ባደረጉት ተከታታይ ጥረት ወታደራዊ የሽግግር ምክር ቤቱና ሲቪል የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳተፉበት የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

በዚህም #ሱዳን ወደ #መረጋጋት እንደምትገባ ተስፋ ተጥሎበታል፡፡ የሽግግር መንግሥቱ ምሥረታ ላይ ለመገኘትም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶክተር) የሚመሩት ልዑክ ዛሬ ጠዋት ካርቱም ገብቷል፤ ደማቅ አቀባበልም ተደርጎለታል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ልዑካቸውን ይዘው ሱዳን ካርቱም ገብተዋል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ለትውልድ ውድቀትና ጥፋትን ማውረስ አይገባም" – ፕሬዚዳንት ኡሁሩ
.
.
የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጳጉሜን 2 እና 3 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በሚካሄደው የሠላም ፌስቲቫል ላይ እንደሚገኙ አስታወቁ።

ፕሬዚዳንቱ ይህን ያስታወቁት ከአገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና ሠላም ኮሚቴ የበላይ  ጠባቂ የቀድሞው ፕሬዚደንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመና ከኮሚቴው አባላት ጋር ባካሄዱት ውይይት ነው። ኡሁሩ ‘ኢትዮጵያዊያን በምንም ሁኔታ ውስጥ ሆነው የማይለወጡና ለድርድር የማይቀርቡ የኬንያዊያን ወዳጆች ናቸው’ ሲሉ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ከቅድመ ነጻነት ጊዜ ጀምሮ የኬንያ የቁርጥ ቀን ወዳጅ እንደሆነች አስታውሰው ጳጉሜን 2 እና 3 ቀን 2011 ዓ.ም በሚካሄደው አገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና የሠላም ፌስቲቫል ‘እንደራሳችሁ እንደ ኢትዮጵያዊያን ሆኜ ነው የምገኘው’ ብለዋል። መሪዎች ለሕዝቦቻቸው ሠላምና ብልፅግናን እንጂ ውድቀትና ጥፋትን ማውረስ አይገባም ሲሉም ተደምጠዋል።

የአገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና ሠላም ፌስቲቫሉን ያዘጋጀውና በበጎ ፈቃድ የተቋቋመው ኮሚቴ አባላት ፕሬዚዳንት ኡሁሩ በፌስቲቫሉ እንዲታደሙ ከጋበዙ በኋላ ከኬንያ ግጭትን የማስወገድ ተሞክሮን እንዲያጋሩ እንደሚፈልግ ገልፀዋል።

የቀድሞው የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ራኢላ ኦዲንጋም በፌስቲቫሉ ላይ እንዲሳተፉ የቀረበላቸውን ግብዣ  ተቀብለው በዝግጅቱ እንደሚገኙ ቃል ገብተዋል።

አገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና ሠላም ኮሚቴ ሠላሟና ልማቷ የተረጋገጠ ኢትዮጵያን ለመፍጠር በሚል ዓላማ ከንግዱ ማኅበረሰብ፣ ከሃይማኖት ተቋማት፣ ከስነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ ከወጣቶችና ከሲቪል ማኅበረሰብ አባላት የተዋቀረ ኮሚቴ ነው።

Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጳጉሜን 2 እና 3 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በሚካሄደው የሠላም ፌስቲቫል ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። #ETHIOPIA #KENYA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሰላም ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው!

በምዕራብ ኦሞ ዞን በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰተውን ግጭትና የሰላም እጦት ለመፍታት የሚያስችል የሰላም ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው። የሰላምና የጸጥታ ኮንፈረንሱ በአካባቢው ለበርካታ ዓመታት የዘለቀው የሠላም ዕጦት መፍትሔ በሚያገኝበት ዙሪያ ላይ ያተኮረ መሆኑም ተመልክቷል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia