TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አዲስ አበባ⬇️

ሰሞኑን ወደ መሬት ባንክ እንዲመለሱ ውሳኔ የተላለፈባቸው የአዲስ አበባ ሰፋፊ ቦታዎች ዳግም በሕገ-ወጥ መንገድ እንዳይወረሩ #ጥበቃ እንዲደረግላቸው ትዕዛዝ ተላልፏል፡፡ የመሬት ባንክና ማስተላለፍ ጽህፈት ቤት ለቦታዎች ጥበቃ እንዲያደርግ ለደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት በደብዳቤ ትዕዛዝ አስተላልፏል ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል...

በሕገ-ወጥ መንገድ #የጋራ መኖሪያ ቤቶችን የያዙ አካላትን #በማጋለጥ ጥቆማ እንዲሰጥ የከተማው ነዋሪ ጥሪ ቀርቦለታል፡፡ ጥሪውን ያቀረበው የአዲስ አበባ አስተዳደር ቤት ኖሯቸውም የጋራ መኖሪያ ቤቶችን የወሰዱ ካሉ፣ ነዋሪው እንዲጠቁመው ይፈልጋል፡፡ የአዲስ አበባ ከንቲባ ፅ/ቤት በፌስቡክ ገጹ እንዳስረዳው፣ ታጥረው የቆዩ የከተማዋን መሬት ወደ መንግስት እንደመለሰው ሁሉ በጋራ መኖሪያ ቤቶችም ላይ ምርመራውን ቀጥሏል፡፡ የቤት ችግር ላለባቸው ነዋሪዎች ታስቦ የተገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በህገ-ወጥ መንገድ በያዙት ላይ፣ በተደረገው #ፍተሻ የተገኘውን ውጤት እንደሚገለፅም ተጠቁሟል፡፡
እስከዚያው ነዋሪዎች፣ ሰው ሳይገባባቸው የቆዩ፣ በህገ-ወጥ መንገድ የተያዙ ቤቶችን እንዲጠቁሙ አሳስቧል፡፡

ምንጭ፦ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በየመንገዱ የሚሸጡ ፀረ ተባይ መድኃኒቶችን ባለመግዛት እና #በማጋለጥ ለሕግ ማቅረብ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

ተጨማሪ የንብቡ👇
https://telegra.ph/AMRS-07-10