TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update CNN⬆️

ዓለም አቀፉ ብዙኃን መገናኛ ሲኤን ኤን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶር. ዐብይ አህመድን
በተመለከተ ሰፊ ትንታኔ አስነብቧል፡፡

#ወጣቱ#ዲሞክራቱ እና #ሰላምን ሰባኪዉ መሪ ኢትዮጵያዉያን ለዘመናት ሲመኙት የነበረ አይነት መሪ መሆኑ በዘገባዉ ተገልጿል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን በመምጣታቸዉ ኢትዮጵያን ከእርስ በርስ ግጭት እና መበታተን ታድገዋል፡፡

በአስተዳደር ቆይታቸዉም እስረኞች ተለቀዋል፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ሰላም ፈጥረዋል፣ የሚዲያ ነፃነትን አዉጀዋል፣ አስቸኳይ አዋጁን አንስተዋል፣ ኢኮኖያዊ ለዉጦችን የተመለከቱ ዉሳኔዎችን አሳልፈዋል፡፡ ከሁሉም በላይ የኢትዮጵያዉያንን ተስፋ አለምልመዋል ብሏል ዘገባዉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተወዳጅነታቸዉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሶ በሃገሪቱ መዲና የጠቅላይ ሚኒስትሩን ምስሎች እና እሳቸዉን የሚደግፉ መልዕክቶች መኪኖች ላይ እና በማህበራዊ ሚዲያዎች ማየት የተለመደ ነዉ ብሏል፡፡ ምስላቸዉን የያዙ ቲሸርቶችም ይሸጣሉ ሲል ገልጿል፡፡

ዶ.ር ዐብይ ከሳቸው በፊት ከነበሩት መሪዎች ልዩ ናቸው ያለዉ #ዘገባዉ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትን በፍቅር ይቀበላሉ፣ ከአድናቂዎቻቸው ጋር #ፎቶግራፍ ይነሳሉ፣ ፈገግታቸውም ለካሜራ ሳይሆን #ከልብ ነው ሲል አስፍሯል፡፡

ቶም ጋርድነር የተሰኘ እንግሊዛዊ ጋዜጠኛን ዋቢ አድርጎ ዘገባዉ እንዳሰፈረዉ ዶር. ዐብይ ከፈጣሪ የተላኩ መሪ ተደርገዉ እንደሚቆጠሩ ገልጿል፡፡

የተወሰኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ነብይ እንደሆኑ ያምናሉም ብሏል፡፡ ዶር. ዐብይ የመበታተን ስጋት ተጋርጦባት የነበረችዉን ሀገር መታደግ ችለዋል ፡፡

መሪዉ #በወታደራዊ አስተዳደር በቂ ልምድ ማካበታቸዉን እና ይህም እንደጠቀማቸዉ አስነብቧል።

ሲኤን ኤን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ደህንነት እና በተለያዩ አካባቢዎች የሚነሱ የመንጋ ፍትህ እንዲሁም ሁከቶች ጥንቃቄ ያሻችዋል ብሏል፡፡

እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሀገራት ዶር. ዐብይን የመሰሉ ሰዎች ከሚሊየን አንድ ናቸዉ ያለዉ ዘገባዉ አፍሪካ ካፈራቻቸዉ ጥቂት ታላቅ መሪዎች አንዱ ሊሆኑ ይችላሉ ሲል ትንታኔዉን ደምድሟል፡፡

ምንጭ፦ ሲኤን ኤን (በአመብድ ወደ አማርኛ ተቀየረ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" የወሰዱትን ገንዘብ እስካሁን ድረስ አልመለሱም " ልያላቸው ግለሰቦችን #ፎቶግራፍ በተለያዩ ሚዲያዎች ማውጣት የቀጠለው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዛሬ ደግሞ  ከ64 ሺህ እስከ 71 ሺህ ብር " ያለአግባብ የወሰዱትን ገንዘብ አልመለሱም " ያላቸውን ገለሰቦች ፎቶግራፍ አሰራጭቷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Anti Money laundering law Amharic from COM to HPR (1).pdf
#ይነበብ🚨

" በወንጀል የተገኘን ንብረት #ህጋዊ_ማስመሰልና #ሽብርተኝነትን_በገንዘብ_የመርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር " የወጣ ረቂቅ አዋጅ ለሕ/ተ/ም/ቤት ቀርቧል።

በዚሁ ረቂቅ ላይ በክፍል 5 ' ስለ ምርመራ '  ሰፍሯል።

ረቂቁ ስለ #ምርመራ ምን ይላል ?

- በወንጀል የተገኘ ንብረት ህጋዊ ማስመሰል ወይም ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ወይም የወንጀል ፍሬን ተከታትሎ ለመለየት #የዳኝነት_አካላት ለተወሰነ ጊዜ፦

በባንክ ሂሳቦች እና በሌሎች ተመሳሳይ ሂሳቦች ላይ #ክትትል_ለማድረግ

የኮምፒዉተር ሥርዓቶችን፣ መረቦችንና ሰርቨሮችን ለመለየት፣

መገናኛዎችን #በክትትል ሥር ለማዋል ወይም #ለመጥለፍ

ድርጊቶችን፣ ባህሪዎችንና ንግግሮችን በድምፅ እና በምስል #ለመቅረፅ እና #ፎቶግራፍ_ለማንሳት

የደብዳቤ ልዉዉጦችን #ለመጥለፍ እና #ለመያዝ

በሽፋን ሥር ስለሚደረግ ምርመራና በቁጥጥር ስር የሚደረግ ማስተላለፍ ለመጠቀም፣

የሚያስችል ትዕዛዝ #ለወንጀል_መርማሪ_አካላት መስጠት ይችላሉ።

- የመርማሪ አካል የተደነገጉትን የማስረጃ ማሰባሰቢያ ዘዴዎችን ተግባራዊ ማድረግ የሚችለዉ ፍርድ ቤት አስተማማኝ ምክንያት መኖሩን በማረጋገጥ #ሲፈቅድ_ብቻ ነዉ።

- መርማሪው አካል #አስቸኳይ_ሁኔታ_ካጋጠመው በአካባቢው ያለውንና የሚመለከተውን የዓቃቤ ሕግ ተቋም የበላይ ኃላፊ በማስፈቀድ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ የምርመራ ዘዴዎችን በመጠቀም ማስረጃዎችን ሊሰበስብ ይችላል፡፡

- መርማሪ አካል #ያለፍርድ_ቤት_ትዕዛዝ የምርመራ ዘዴዎችን ተጠቅሞ ማስረጃ ለመሰብሰብ በጀመረ በ፵፰ ሰዓት ውስጥ ምክንያቶቹንና በዓቃቤ ሕግ የተሰጠውን ጊዜያዊ ፈቃድ ጨምሮ ለፍርድ ቤት በፅሁፍ ማቅረብ ይኖርበታል። ፍርድ ቤቱ የጥያቄውን አግባብነት መርምሮ ለመቀበል ወይም ደግሞ ውድቅ ለማድረግ ይችላል፡፡

- ፍርድ ቤት የምርመራ ዘዴ ማስረጃ እንዲሰበስብ ለመርማሪ አካል ፈቃድ ሲሰጥ፡-
ሀ. ማስረጃ ስለሚሰበሰብበት ዘዴ እና ስለሚከናወንበት አግባብ፤
ለ. የሚከናወንበት ጊዜ በተመለከተ ተገቢውን ትዕዛዝ መስጠት አለበት፡፡

- የማስረጃ ማሰባሰቢያው ዘዴ ጠለፋ ወይም ክትትል እንደሆነ #ጠለፋዉ ወይም #ክትትሉ የሚደረግበትን የስልክ ፣ የፋክስ ፣ የሬዲዮ ፣ የኢንተርኔት ፣ የኤሌክትሮኒክስ ፣ የፓስታና የመሳሰሉትን የግንኙነት መስመሮች አድራሻ ወይም መለያ መጥቀስ አለበት፡፡

- ማንኛውም የመገናኛ አገልግሎት አቅራቢ በመርማሪ አካል ጠለፋውን ለማካሄድ ሲጠየቅ ጠለፋው በፍ/ቤት ወይም በአቃቤ ሕግ የበላይ ሃላፊ የተፈቀደ መሆኑን በማረጋገጥ አስፈላጊውን ትብብር ማድረግ አለበት፡፡

- በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሃገር በሕግ አስከባሪ አካላት በጠለፋ የተገኘ ለጉዳዩ አግባብነት ያለው ማስረጃ #በጠለፋ_በተገኘበት_መልክ_በቀጥታ ካልቀረበ በቀር ዋጋ አይኖረውም፡፡

ሙሉ ረቂቅ አዋጁን በዚህ ያንብቡ 👇 https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/88222

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia