TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሹመት🔝

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር ክብር አቶ #ገዱ_አዳርጋቸው ለሁለት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ሹመት መስጠታቸው
ተገለጸ ፡፡

ሹመቱ የተሰጣቸው የስራ ኃላፊዎች አቶ #ዮሐንስ_ቧያለው እና አቶ #አለባቸው_የሱፍ ናቸው፡፡

አቶ ዮሐንስ ቧያለው ከህዳር ሰባት ቀን 2011 ዓ.ም ጀምረው በርዕሰ መስተዳደሩ ጽ/ቤት የበይነ መንግስታት ግንኙነት ቢሮ ኃላፊ ሆነው እንዲያገለግሉ ተሹመዋል፡፡

አቶ አለባቸው የሱፍ ደግሞ ከህዳር አንድ ቀን 2011 ዓ.ም ጀምረው የዚሁ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሆነው እንዲያገለግሉ መሾማቸው ታውቋል፡፡

አቶ ዮሐንስ ቀደም ሲል በመንግስት የተለያዩ ኃላፊነቶች ሲሰሩ መቆየታቸውና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም በመምህርነት እያገለገሉ ነበር፡፡

አቶ ዮሐንስ ቧያለው በቅርቡ ብአዴን 12ኛ ድርጅታዊ ጉባዔውን አካሄዶ ስሙን ወደ አማራ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (አዴፓ)ሲቀይር የድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ሆነው እንደተመረጡ ይታወሳል፡፡

አቶ አለባቸው የሱፍም በተለያዩ የመንግስት የስራ ሓላፊነቶች በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡

ምንጭ፦ የርዕሰ መስተዳደር ጽ/ቤት(Amhara Democratic Party /ADP/ CC office)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አቶ #ገዱ_አዳርጋቸው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር በመሆን በእጩነት ቀረቡ። #ebc

@tsegabwolde @tikvahethiopia