TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ስለ ጉራጌ ዞን ከDW⬇️

በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ በምትገኘው ኢንሴኖ ከተማ በተቀሰቀሰ ግጭት #በርካታ ሰዎች መሞታቸውን የአይን እማኞች ተናገሩ። የአይን ዕማኝነታቸውን ለDW የሰጡ የአካባቢው ነዋሪ የማረቆ ወረዳ ዘጠኝ ቀበሌዎች ወደ መስቃን ወረዳ መካከላቸውን በመቃወም ከትናንት በስቲያ ሐሙስ በተቀሰቀሰ ግጭት ከ20 በላይ ሰዎች ሞተዋል። አንድ የአካባቢው ባለስልጣንም ግጭት #መፈጠሩን እና ሰዎች #መሞታቸውን አረጋግጠዋል። 

በማረቆ ወረዳ ቆሼ ከተማ የሚኖሩ የአይን ዕማኝ በሰዎች ላይ ጥቃት ሲፈጸም፣ የመኖሪያ ቤቶች #ሲቃጠሉ መመልከታቸውን አስረድተዋል። "ጥቃቱን ለማስቆም ብንሞክርም አልተሳካልንም" ያሉት የአይን እማኙ "በሁለት ቀናት ሐሙስ እና አርብ ግፋ ቢል #ከ20 ያላነሰ ሰው ሞቷል። በማረቆ ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ የሟቾችን አስከሬን አሁን አንቡላንስ እየሰበሰበው ይገኛል። ግማሹ በወራጅ ወሐም ተወርውሯል" ሲሉ አስረድተዋል።

የማረቆ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ በለጠ ደራሮ ግጭቱ "የግል ፍላጎት ባላቸው አካላት እንደተቀሰቀሰ" ተናግረዋል። ግጭቱ "በመስቃን እና በማረቆ" መካከል የተፈጠረ አይደለም ያሉት አቶ በለጠ "መነሻው አልገባንም" ሲሉ ለDW አስረድተዋል። "በሰውም ላይም ጉዳት ደርሷል። በንብረትም ላይ ከፍተኛ የሆነ ጉዳት ደርሷል። በማረቆ አካባቢ በርካታ መስቃኖች አሉ። ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰባቸውም። ሽማግሌዎቹ፤ አመራሮቹ እነሱን መንካት እኛን መንካት ነው። እነሱ አልበደሉንም በስመ መስቃን ማንም መነካት የለበትም በሚል በትክክል ሐብቱ የሰው ማንነቱ ተከብሮ የመስቃን ተወላጅ ምንም አልተደረገም። የማረቆ ተወላጅ ግን መስቃን ውስጥ ጥቃት እየደረሰበት ነው። በንብረቱም ላይ በሕይወቱም ላይ ከፍተኛ ጥቃት እየደረሰበት ነው" ሲሉ ተናግረዋል። በግጭቱ ምን ያክል ሰዎች እንደሞቱ የተጠየቁት አቶ በለጠ "ይኸን ያህል የሚል የለንም። እየለየን ነው ያለንው" ሲሉ ተናግረዋል።

አቶ በለጠ "የመንግሥት አካላት ሰራዊት በመላክ ጉዳዩ እየረገበ ነው። ልዩ ኃይሎችም አሉ። መከላከያዎችም አሉ። እነዚህ ንብረትም ሕይወትም የማዳን ሥራ ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ከህዝቡ ጎን በመቆም ከዱርየው ጥቃት ሕዝቡን እያዳኑ ነው ያሉት" ሲሉ አክለዋል።

የቆሼው ከተማ ነዋሪ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እና የጸጥታ አስከባሪዎች በአካባቢው መሰማራታቸውን ገልጸዋል። "የጸጥታ አስከባሪዎች ወደ ቦታው ከተሰማሩ በኋላ የሰው ሕይወት እየጠፋ አይደለም" ያሉት አቶ በለጠ በበኩላቸው ውጥረቱ አሁንም እንዳልረገበ አስረድተዋል። ግጭቱ የተቀሰቀሰባት #የኢንሴኖ ከተማ ከአዲስ አበባ በ211 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘው ቡታጅራ አቅራቢያ ትገኛለች። በጉራጌ ዞን ሥር የሚገኙት መስቃን እና ማረቆ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በአንድ ወረዳ ሥር ይተዳደሩ ነበር።

©የጀርመን ድምፅ ሬድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ለዓለም ዋንጫ ታልፍ ይሆን ?

የኢትዮጵያ #ከ20_ዓመት_በታች ሴት ብሔራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር የመልስ ጨዋታውን ከሞሮኮ አቻው ጋር በአዲስ አበባ ፤ አበበ ቢቂላ ስታዲየም እያደረገ ይገኛል።

ብሔራዊ ቡድኑ ከሳምንት በፊት ከሜዳው ውጪ ያደረገውን የማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታ በሞሮኮ የ2ለ0 ተሸንፏል።

ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታውን በድምር ውጤት የሚያሸንፍ ከሆነ በቀጥታ ኮሎምቢያ ለምታዘጋጀው የ2024 ዓለም ዋንጫ ውድድር ያልፋል።

በ " አበበ ቢቂላ ስታዲየም " እየተካሄደ ያለውን ጨዋታ በቲክቫህ ስፖርት መከታተል ይችላሉ ፦ https://publielectoral.lat/+VvwzStMNcNHmhK0x

በተጨማሪ በቀጥታ ለመመልከት ፦ https://www.youtube.com/live/fGyiYbhaj-k?si=_DGAQyXg1Oo7q5u_

ፎቶ ፦ የኢትዮጵያ እና የሞሮኮ እግር ኳስ ቡድን አባላት (Tikvah Ethiopia Sport Image)

@tikvahethiopia @tikvahethsport    
TIKVAH-ETHIOPIA
“ ባለፈው ሳምንት ብቻ 7 ሰዎች ናቸው የተገደሉት ” - ነዋሪዎች በኮሬ ዞን ፤ #በታጣቂዎች አማካኝነት ንጹሃን ላይ የሚደርስ ጥቃት በእርቀ ሰላም ተፈቶ ቆሞ የነበረ ቢሆንም ከ4 ወራት ወዲህ በማገርሸቱ የንጹሐን ግድያ፣ የንብረት ዘረፋ እየተፈጸመ መሆኑን የዞኑ ባለስልጣትና ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። መንግሥት መፍትሄ እንዲሰጥም ተጠይቋል። ባለስልጣናቱና ነዋሪዎቹ ለድርጊቱ  የ " ኦነግ…
#ኮሬ

° " የንጹሀን ሞት ይቁም፤ገዳዮች ለፍትህ ይቅረቡልን !! " - የዳኖ ቀበሌ ነዋሪዎች

° " በግጭቱ ሁለት ሰዎች ሲጎዱ የአንደኛው ህይዎቱ አልፏል " - የኮሬ ዞን የሰላምና ጸጥታ ሀላፊዉ ተፈራ ቦንዶሮ

በኮሬ ዞን ፤ ዳኖ ቀበሌ ከትናንት ጀምሮ የደረሰ በቆሎ ታጥቀው በመጡ አካላት በመጨፍጨፉ ምክንያት በተነሳው ግጭት የሰው ህይወት አልፏል።

የአካባቢው ነዋሪዎች ይህ ድርጊት ታጥቀው ከምዕራብ ጉጂ ዞን ጋላናና ሱሮ ባርጉዳ ወረዳ ቀበሌያት ወደ ኮሬ ዞን ዘልቀው በገቡ አካላት ነው የተፈጸመው ብለዋል።

እነዚሁ ታጣቂዎች " ከዚህ ቀደምም ከብቶች ሲነዱብን አርሶአደሮች ሲገደሉብን ቆይተዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

በዚህ አመት ብቻ #ከ20_በላይ ሰዎች መሞታቸውን አስረድተዋል።

በመሆኑም " እነዚህን አካላት መንግስት አስታግሶ ለህግ / ለፍትህ ያቅርብልን ፤ የንጹሀን ሞት ይቁም ፤ ሰሚ በማጣታችን እሄዉ ዛሬም ግጭቱ ቀጥሏል " ብለዋል።

በአካባቢው ያለዉ ተኩስም የታጠቁ አካላትን ወሰን አልፈዉና ወደመንደሩ ተጠግተዉ የጀመሩት ነው ሲሉ አስረድተዋል።

ይህን ጉዳይ በተመለከተ ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የኮሬ ዞን የሰላምና ጸጥታ ሀላፊዉ ተፈራ ቦንዶሮ ፥ (ቃላቸውን በሰጡበት ሰዓት / ከሰዓት ) አካባቢው ላይ ከባድ ተኩስ እንደነበር ገልጸዋል።

ግጭቱን ለማርገብ ርብርብ ላይ በመሆናቸዉ ምላሽ ለመስጠት አይመችም ቢሉም ቆይተዉ የተብራራ ምላሽ ሰጥተዋል።

ከምዕራብ ጉጂ ዞን የመጡ ታጣቂ ሀይሎች አካባቢው በመመንጠርና የበቆሎ ማሳዎችን በመጨፍጨፋቸው ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር ግጭት ውስጥ መግባታቸውን ገልጸዋል።

በግጭቱ አንድ ሰው #ሲሞት ፤ አንድ ሰው ቆስሏል ብለወል።

ግጭቱን በቀሰቀሱት በኩል የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ የሚያዉቁት ነገር እንደሌለ ገልጸው አሁን ላይ አካባቢዉ መረጋጋቱን ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለዘላቂ ሰላም ምን ታስቧል ? ሲል ጠይቋል።

እሳቸውም ፤ ከአካባቢው በተወሰነ ርቀት ላይ የሀገር መከላከያ ሀይሎች እንደሚኖሩና ከሚቆጣጠሩት ቦታ በተጨማሪ የታጠቁ ሀይሎች የሚመጡበትን መንገድ እንዲቆጣጠሩ ለመነጋገር ማሰባቸዉን ገልጸዉ ይህ ግን በመከላከያው ፈቃድና የስምሪት ሁኔታ የሚወሰን ነው ብለዋል።

ግጭቱ ያለበት የኮሬና ጉጂ ማህበረሰብ መሀከል በአካባቢዉ ባህል መሰረት የእርቅ ስርዓት በተደጋጋሚ ቢካሄድም ዕርቁ ውጤታማ ሳይሆን መቅረቱን ለማወቅ ችለናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ በምዕራብ ጉጂ ዞን በኩል ምላሽ ለማግኘት ሙከራ ቢያደርግም አልተሳካም ፤ ከዚህ ቀደምም ሙከራ ቢደረግም ምላሽ ሰጪ አልተገኘም። አሁንም ምላሽ አለኝ የሚል ምላሹን መስጠት ይችላል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia