TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሻሸመኔ
#ሀዋሳ
#ነቀምት
#አሰላ
#አዲስአበባ
#ሽሬ
#ደብረብርሃን
#ወላይታሶዶ
#አርባምንጭ
#ጅግጅጋ
#አዳማ
#ድሬዳዋ
#ባህርዳር
#መቐለ
#ሀረር
#ጎንደር

ከሌሎች በርካታ ከተሞች ከሚገኙ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች የSAT ውጤት ያልጠበቁት እንደሆነ በመግለፅ ቅሬታቸው እያሰሙ ይገኛሉ። የሚመለከተው አካል ማብራሪያ እንዲሰጥበትም ጠይቀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አምቦ #ለኩ #ጅማ #ከሚሴ #ይርጋለም #ሃዋሳ #ሶዶ

ኑ ትውልድ እንገንባ!

#አዲስ_አበባ
0970514616/ዮናስ ገ/መስቀል/
0924140293/መባ/

#ሰበታ
0932540523/ያሬድ ለማ/
0921421493/ያብስራ ካሳ/

#መቐለ
0912178520/ኤርሚያስ ደጀኔ/
0923602445/ፊራኦል መስፍን/

#ራያ_ቆቦ
+251949256094/ሉላይ/

#ጅማ
0911670454/አሰፋ/

#ድሬዳዋ
0915034762/መሃሪ/

#አዳማ
0949377735/ሰላም/

#ሀዋሳ
+251926429534/ተስፋ/
+251935932153/ብስራት/

#ለኩ
0919687777/ዳዊት እንዳለ/

#ይርጋለም
0953804369-/አሸናፊ/
0964039768-ብርሀኑ/

#ከሚሴ
0915543171/ሁሴን/

#ወላይታሶዶ
+251913776084/Aso/
0926172318/Beza/

•ከ1ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ መደበኛ የመማሪያ እና አጋዥ መፅሃፍትን በመለገስ ለመጭው ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን እናውርስ!!

📚የዘንድሮው አመት ተፈታኝ ተማሪዎች እና ወላጆች በዚህ ስራ ላይ በስፋት በመሳተፍ ለመጭው ትውልድ አርዓያ ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን!

5ኛው አመት የTIKVAH-ETHIOPIA የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ!

በዚህ ሀገራዊ ስራ መሳተፍ የምትፈልጉ የበጎ አድራጎት ማህበራትና ግለሰቦች @tsegabwolde

በሁሉም ከተሞች ያሉ አስተባባሪዎችን በየዕለቱ እናሳውቃለን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ወላይታሶዶ

ከፍተኛ የዞን አመራሮች የተሳተፉበት የደብተር ማሰባሰብ ዘመቻ!

ባለፈው ሳምንት "አለን ኢትዮጵያ ወላይታ ሶዶ" ከተለያዩ የበጎ አድራጎት ማህበራት ጋር በመሆን ለ800 ተማሪዎች የሚውል ጠንካራ የትምህርት ቁሳቁስ ማሰባሰብ ዘመቻ አካሂዶ ነበር። በዚህም የደፍተርና የ እስኪብርቶ ማሰባሰብ ፕሮግራም፦

•የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኩምቤ
•የየዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ፍሬው
•የዞኑ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ፀጋ
•የከተማዉ ካንቲባ አቶ ሀንጃላ
•የዞኑ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ በረከት
•የዞኑ የወጣቶች ሊግ ፕሬዝዳንት አቶ ሚካኤል
•የከተማው የወጣቶች አደረጃጀት አመራሮች እንዲሁም ሌሎች ባለሥልጣናት ተገኝተው ደብተርና እስኪብርቶ በመለገስ የወጣቶቹን መልካም ተግባር በመደገፍና ሀገራዊ ግዴታን በመፈፀም በ "አለን ኢትዮጵያ የሰው ልጆች የለውጥ ማዕከል" ጎን በመቆም የላለሳለሰ ድጋፍ አድርገዋል።

Via አለን ኢትዮጵያ ከወላይታ ሶዶ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ወላይታሶዶ_ዩኒቨርሲቲ

• " ለጉልበት ሰራተኞች 4 ሚሊዮን ብር ተከፍሏል ቢባልም ገንዘብ መውጣቱን እንጂ #የት_እንደገባ ማረጋገጥ አልተቻለም " - የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲን የ2013 በጀት ዓመት የሒሳብ ህጋዊነት ኦዲት ሪፖርትን ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ገምግሟል።

በዚህ ግምገማ ምን ተባለ ?

- ዩኒቨርሲቲው የኦዲት ግኝቱን የማስተካከያ እርምጃ እየወሰደ ባለመሆኑ ባለፉት አራት ዓመታት ተቀባይነት የሚያሳጣ የኦዲት አስተያየት ውስጥ ያለፈ ተቋም እንደሆነና በትኩረት መስራት እንዳለበት ቋሚ ኮሚቴው አስገንዝቧል።

- ዩኒቨርሲቲው ማስመለስ ከነበረበት የገንዘብ ምጣኔ 99.95% እንዳላስመለሰ እና የኦዲት ግኝት መስተካከል ከነበረበት 11 ጉልህ  የኦዲት ግኝቶች 1 ብቻ ምላሽ እንዳገኘ ኮሚቴው ገልጿል።

- የዩኒቨርሲቲው አመራር የፋይናንስ ህግጋትን እና አሰራሮችን ተከትሎ ከመስራት አኳያ ሰፊ ክፍተት በመኖሩ በትኩረት መስራት አለበት ተብሏል።

- ዩኒቨርሲቲው ባልተሰጠው ስልጣን አዳዲስ ደንቦችን እና መመሪያዎችን እያዘጋጀ ክፍያ ሲፈፅም የነበረ ሲሆን #ለጉልበት_ሰራተኞች አራት (4) ሚሊዮን ብር ተከፍሏል ቢባልም ገንዘብ መውጣቱን እንጂ የት እንደገባ ማረጋገጥ እንዳልተቻለ ኮሚቴው ገልጿል።

የኦዲት ግኝቶችን በተመለከተ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ክርስትያን ታደለ ምን አሉ ?

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተሻሻለ የኦዲት ግኝት ማሻሻያ መርሃ-ግብሩን እስከ መጋቢት 23/2015 ዓ.ም እንዲያቀርብ እና መርሃ-ግብሩም ፦
- ለገንዘብ ሚኒስቴር፣
- ለፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት እና ለሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ግልባጭ ሪፖርት ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ተቋሙ የኦዲት ግኝቶችን ትኩረት ሰጥቶ ተገቢውን የእርምት ዕርምጃዎችን እየወሰደ በየ 3 ወሩ ለቋሚ ኮሚቴው ሪፖርት ማቅረብ አለበት ብለዋል።

አያይዘውም ገንዘብ ሚኒስቴር ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ባልተወጡ የዩኒቨርሲቲው #አመራሮች እና የሥራ ኃላፊዎች ላይ አስተዳደራዊ ዕርምጃዎችን ወስዶ ሪፖርቱን በ10 ቀናት ውስጥ ማሳወቅ እንደሚገባው አስገንዝበዋል።

የፍትህ ሚኒስቴር #በወንጀለኛ እና #በፍትሃብሄር ተጠያቂነት የሚያስከትሉ ጉዳዮች ካሉ መርምሮ ክስ መመስረት እንዳለበት አቶ ክርስቲያን ታደለ አስረድተዋል።

አቶ ክርስትያን የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኦዲት ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ ተገቢውን የቁጥጥር ስራ እንዲሰራ እና የኦዲት ግኝቶች ዩኒቨርሲቲው የእቅድ አካል አድርጎ እንዲያካትታቸው ተገቢውን አመራር  እንዲሰጥ አሳስበዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከስልጣኑ ውጪ ባወጣቸው ደንቦች እና መመሪያዎች የሚያደርጋቸውን ክፍያዎች እንዲያቆም እና በቀጣይም በመንግስት የፋይናንስ ህግጋት እና መመሪያዎች ተንተርሶ ብቻ መስራት እንዳለበት፤ ያለ አግባብ የተከፈሉ ክፍያዎችም ተመላሽ እንዲሆኑ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

#FDRE_HoPR

@tikvahethiopia