TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጉዞ ሉሲ~ለሰላምና ለፍቅር!

‹‹ጉዞ ሉሲ ለሰላምና ለፍቅር መርሀ-ግብር›› ትላንት ምሽት በሚሊኒዬም ተጀምሯል፡፡ በዝግጅቱ መክፈቻ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኢፌዴሪ ባሕልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር #ሂሩት_ካሰው ‹‹ዘረኝነት፣ መለያዬት፣ ማግለልና ንፉግነት የኛ የኢትዮጵያዊነት ባሕል አይደለም፡፡ ከዛሬ ጀምሮ የነበረንን መተዛዘን፣ #ፍቅርና #አንድነት ወደ ነበረበት እንዲመለስ ለውጥ የሚጀምረው ከራስ ነውና ለለውጥ እዘጋጃለሁ፤ ለለውጥ እንዘጋጅ›› በሚል #የአንድነት ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

በመርሀ-ግብሩ ከአፋር ክልል ጀምሮ በተለያዩ ክልሎች ሉሲ የአምስት ቀናት ቆይታ እያደረገች ሕዝቡ #በአንድነቱ ዙሪያ እንደሚወያይ የገለጹት ሚኒስትሯ ‹‹ሉሲንና ሌሎች አንድ የሚያደርጉን በዩኔስኮ የተመዘገቡ ቅርሶችን በታላቅ ክብር ከብሔራዊ ሙዚዬም ወደ ፓርላማ አጓጉዘን ወደ አፋር በመሸኘት ይጀመራል›› ነው ያሉት፡፡

ሉሲ የእገሌ የሚባል ሃይማኖት፣ ብሔር፣ አስተሳሰብ ወይም ሌላ #ወካይ_ያልሆነች የሁሉም የሰው ዘር ግንድ መሆኗን የጠቀሱት ሚንስትሯ ‹‹ደግነትና አብሮነት ስላልተለየን በጎ ትሩፋት ሳይሠራ የሚውል #ኢትዮጵያዊ የለም፡፡ የትኛውም ኢትዮጵያዊ የተራበ ሳያበላ፣ የተጠማ ሳያጠጣ፣ የወደቀ ሳያነሳ፣ የሞተ ሳይቀብር አይውልም፤ ኢትዮጵያዊነትም ይህ ነው›› ብለዋል፡፡ እንኳን እርስ በእርስ ከሌላውም ዓለም ጋርም ኢትዮጵያዊ በሉሲ የተዛመደ መሆኑንና #ዘረኝነት የኢትዮጵያዊነት ባሕል አለመሆኑን ነው ዶክተር ሂሩት ያስገነዘቡት፡፡

በመርሀ-ግብሩ መክፈቻ ዝግጅት በአዲስ አበባ ሚሊኒዬም አዳራሽ አንጋፋና ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ዝግጅቶቻቸውን አቅርበዋል።

Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአንድነት ጥሪ ለመላው ኢትዮጵያዊያን!

‹‹ዘረኝነት፣ መለያየት፣ ማግለልና ንፉግነት የኛ የኢትዮጵያዊነት ባሕል አይደለም፡፡ ከዛሬ ጀምሮ የነበረንን #መተዛዘን#ፍቅርና #አንድነት ወደ ነበረበት እንዲመለስ ለውጥ የሚጀምረው ከራስ ነውና ለለውጥ እዘጋጃለሁ፤ ለለውጥ እንዘጋጅ›› ዶክትር #ሂሩት_ካሳው

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እኛስ

የጥንት አባቶቻችን ያለብሄር፣ ያለዘር፣ ያለቋንቋ፣ ያለሀይማኖት ልዩነት ወራሪውን የጣልያን ጦር አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው፤ በደም በአጥንታቸው ይህቺን ሀገር #አስከብረው ለኛ #አስረክበውናል

የዛሬዎቹ ትውልዶች እኛስለቀጣዩ ትውልድ ምን ይሆን የምናወርሰው? የትኛዋን ሀገር ነው የምናወርሰው?

ወገኖቼ ለመጪው ትውልድ ክፍፍል እናውርስ? አንድ የሚያደርገንን ሰውነትን ረስተን በብሄር መቧደንን ለልጆቻችን እናውርስ? ንገሩኝ...በዘር መከፋፈልን እናውርስ? አለመከባበርን እናውርስ?? መሰዳደብን እናውርስ? ቁጭ ብሎ ማውራትን እናውርስ? አለመደማመጥን እናውርስ?

ቆይ ምን ሰርተን አለፍን እንበል

አድዋ የነፃነት ምልክት ብቻ አይደልም፤ አድዋ የኢትዮጵያዊያን #አንድነት እና ጠንካራ #ትስስር መገለጫም ጭምር ነው።

አድዋን ስናከብር...እኛስ ለቀጣዩ ትውልድ ምን እናውርስ? እኛስ ለኢትዮጵያ ምን ሰርተን እንለፍ? የሚሉትን ጥያቄዎች እራሳችንን #እየጠየቅን መሆን አለበት።

በTIKVAH-ETH ስም ሁላችሁንም እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ!

ሰላም፤ ፍቅር፤ አንድነት!
#Adwa123 #አድዋ123
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"እኛ ኢትዮጵያዊያን በየትኛውም መንግሥት፣ በየትኛውም መሪዎች ዘመን ከልዩነት ይልቅ #አንድነት፣ ከግል ጥቅም ይልቅ የሃገርን የምናስቀድም፣ #ከከፋፋይ አሉባልታ ይልቅ ስለ አንድነትና የጋራ እሴቶቻችን የምንገዛ ታላቅ እና ኩሩ ሕዝቦች ነን። ለዚህም አንዱ ምስክር የአባቶቻችን፣ የአያቶቻች ገደል ነው።" ኢ/ር ታከለ ኡማ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#StopHateSpeech-ኩልፎ ካምፓስ👆

#በኩልፎ_ካምፓስ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ከTIKVAH-EHT ጋር በመተባበር ያዘጋጀው #የStopHateSpeech የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። የStopHateSpeech አስተባባሪዎችን #ቴዎድሮስ_ዮሴፍ የተማሪዎች አገልግሎት ኃላፊ እንኳን ደህና መጣችሁ ብለው ተቀብለዋል። በዝግጅቱ ላይ ዶ/ር #ይስሀቅ_ከቸሮ የኮሌጅ ዲን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፤ የተቋማቸው ተማሪዎች የሀገሪቱን #አንድነት ከሚሸረሽሩ ግለሰቦች ጋር #መታገል እንዳለባቸዉ እና በቀጣይም የሀገሪቱ እጣ ፈንታ #በወጣቶች ላይ መሆኑን አውቀው የሚዲያ አጠቃቀማቸውን እንዲያስተላካክሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ማስታወሻ🗓በነገው ዕለት #ተመሳሳይ መድረክ #በአባያ_ካምፓስ ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ የሚካሄድ ይሆናል!! #አርባምንጭ_ዩንቨርስቲ

የአርባምንጭ ተማሪዎች ተቀላቀሉ👇 @tikvahethamu @tikvahethamu

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ህብረ ብሄራዊቷን ኢትዮጵያ አትፈልጓት እኛ ውስጥ ናት ይሏችኃል የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች! #ሰላም #ፍቅር #አንድነት

ከፈጣሪ ቀጥሎ ኢትዮጵያን የሚታደጓት እኚህ👆ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል #የተሰባሰቡ የፍቅር እና የሰላም አምባሳደር ወጣቶች ናቸው።

የሀገሬ ሠዎች አትስጉ፤ ተስፋም አትቁረጡ በፍቅር አትዮጵያን ትልቅ እናደርጋታለን!! አርማችን ነጩ የሰላም ምልክት!!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የአንድ እናት ልጆች ነን መስመር አይለየን...
የአንድ ቤት ልጆች ነን መስመር አይለየን...

#መቐለ_ዩኒቨርሲቲ የሰላም አምባሳደር!
#ፍቅር #ተስፋ #አንድነት #መቐለ_ዩኒቨርሲቲ
#አዲስ_አበባ: "መልካም ወጣት ለኢትዮጵያ #አንድነት 2011" የተሰኘ በአገልጋይ #ዮናታን_አክሊሉ የሚዘጋጅ የወጣቶች መርሃ ግብር #በትላንትናው ዕለት በሚሊኒየም አዳራሽ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በተገኙበት መከፈቱ ተሰምቷል። በመክፈቻ ስነ ስርዓቱ ላይ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እና የገቢዎች ሚንስትር ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ተገኝተው ነበር።

🗞ቀን ሃምሌ 4/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት የድጋፍና የልማት ማህበር አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት እገዛችንን ከፈለገ ከጎኑ እንቆማን አለ፡፡
.
“የደርግ ሰራዊት” የሚለው የበፊት መጠሪያው “የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት” በሚል ተቀይሮ ከመንግስት እውቅና እንደተሰጣቸውም የማህበሩ መሪዎች ተናግረዋል፡፡ “አሁንም የኢትዮጵያን #አንድነት ለማስጠበቅ ከቆመ መንግስት ጋር አብረን ለመስራት ዝግጁ ነን” ብለዋል፡፡

በመላው አገሪቱ 53 ቅርንጫፎች እንዳሉት ተነግሯል፡፡ የማህበሩ ሀላፊዎች በአጠቃላይ ከ1 ሚሊዮን በላይ አባላት አሉት ማለታቸውን ከጋዜጣዊ መግለጫው ሰምተናል፡፡ ማህበሩ ከቀድሞዎቹ ሚሊሺያዎች እስከ ከፍተኛ የጦር መኮንንነት የደረሱ አባላት እንዳሉት ተነግሯል፡፡

ምንጭ - ሸገር 102.1 ኤፍ ኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የዕለቱ መልዕክት፦

ከጭፍን ጥላቻ መላቀቅ ይቻላል!

አብዛኞቹ ሰዎች ጭፍን ጥላቻን በመሠረተ ሐሳብ ደረጃ የሚያወግዙ ቢሆኑም ከጭፍን ጥላቻ መዳፍ የሚላቀቁ ግን ጥቂቶች ናቸው። እንዲያውም ሥር የሰደደ ጭፍን ጥላቻ ያላቸው ብዙ ሰዎች ጥላቻ እንደሌላቸው ሊናገሩ ይችላሉ። ሌሎች ደግሞ ሰዎች ጭፍን ጥላቻቸውን ይፋ እስካላወጡ ድረስ ምንም ጉዳት የለውም ይላሉ።

ይሁን እንጂ ጭፍን ጥላቻ ሰዎችን የሚጎዳና የሚከፋፍል መጥፎ ነገር ነው። ጭፍን ጥላቻ የድንቁርና ልጅ ነው ቢባል የልጅ ልጁ ደግሞ ጠላትነት ነው። ቻርልስ ካለብ ኮልተን የተባሉት ደራሲ (1780-1832) “አንዳንድ ሰዎችን ስለማናውቃቸው #እንጠላቸዋለን። ስለምንጠላቸውም #ልናውቃቸው አንችልም” ብለዋል። ጭፍን ጥላቻን ሰዎች መማር እንደሚችሉ ሁሉ ማስወገድም ይችላሉ።

Via #JW

#ፍቅር #ሰላም #አንድነት #ተስፋ #ኢትዮጵያ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA💪ክብር ይገባችኃል!

ስንተባባር በአንድነት ስንቆም ምንም ነገር አያቅተንም!! 6710 የልብ ህሙማን ህፃናትን አለንላችሁ እንበላቸው!!

#TIKVAH_ETHIOPIA_FAMILY

Screenshot ወደዚህ ግሩፕ👇

https://publielectoral.lat/joinchat/FCD9AhWFZJX_rX95-4rWNQ

#አንድነት #ተስፋ #መተሳሰብ #ፍቅር #ቲክቫህ
❤️ከ3000 በላይ አባል❤️

6710 ላይ የህፃናት የልብ ህክምናን ለማገዝ በተከፈተው ግሩፕ ላይ እስካሁን ከ3 ሺህ የሚበልጡ የቤተሰባችን አባላት ተቀላቅለውናል!! በሺዎች የሚቆጠር ገንዘበ እንደ አቅማችን አስተዋፆ እያደረግን እንገኛለን!! ሀገር ወዳድነት መገለጫው ይህ ነው!!

Screenshot ወደዚህ ግሩፕ👇

https://publielectoral.lat/joinchat/FCD9AhWFZJX_rX95-4rWNQ

እኔ ካለኝ ላይ አካፍያለሁ?? እናተስ??

ለአንድ መልዕክት የሚቆርጠው 1 ብር ብቻ ነው!!


በትንሹ 3 መልዕክት ይላኩ!

#አንድነት #ተስፋ #መተሳሰብ #ፍቅር #ቲክቫህ
#UnityPark

መደበኛ የክፍያ ጉብኝት ከነገ ሰኞ ይጀምራል!

ከነገ ሰኞ ማለትም ከጥቅምት 3 2012 ጅምሮ ማንኛውም ዜጋ 200 ብር እንዲሁም በቪአይፒ (VIP) 1 ሺህ ብር በመክፈል ቤተ መንግስቱን መጎብኘት ይችላል።

የአንድነት ፓርክን ለመጎብኘት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ ይዞ መገኘት ሲኖርበት በተጨማሪም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ቅድመሁኔታዎች ካላሟሉ ፓርኩን መጎብኘት አይችሉም።

ጎብኚዎች ይዘው መምጣት የሌለባቸው ነገሮች፦

- ስለት
- ተቀጣጣይ ቁሶች
- የጦር መሳሪያዎች
- ምግብ መጠጦች እና ጣፋጭ ነገሮች
- ማስቲካ
- የመዋቢያ ቁሶች
- የግል ካሜራዎች
- ስልኮች ታብሌቶች እና ማንቸውንም የምስልና ድምጽ መቅረጫ መሳሪያዎችን
- ሲጋራ እና አደንዛዥ ዕጾች

በፓርኩ ውስጥ ማድረግ የተከለከሉ ተግባራትና ባህሪያት፦

- መጮህና መረበሽ
- ከአስጎብኚ ውጪና ከተመደቡበት የጉብኝት ቡድን ውጪ መንቀሳቀስ
- በታሪካዊ ህንጻዎቹ ላይ መደገፍ
- ቅርሶችንና እንስሳትን መነካካት
- እንስሳትን ከተፈቀደው ቦታ ውጪ መቅረብ
- እንስሳትን መመገብ
- እንስሳትን ማስቆጣት (ጠጠር መወርወር፣ በአካላዊ እንቅስቃሴ ማስፈራራት፣ አላስፈላጊ ድምጽ ማውጣት)
- ከተቀመጡ የቆሻሻ ማስወገጃ እቃ ውጪ ቆሻሻ መጣል
- ሲጋራና ሌሎች አደንዛዥ እጾችን መጠቀም
- የቤት እንስሳትን ይዞ መምጣት
- መንገድ ከተበጀለት ዉጪ መራመድ እና አጥሮችን ከልክ በላይ መጠጋትም ሆነ መደገፍ
- ማንኛዉንም በፓርኩ የሚገኝ የኤሌትሮኒክስ ቁስ ያለፍቃድ መንካት

#አንድነት_ፓርክ
#UnityPark

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ #በጳጉሜ_ወር ለሀገር ሰላም እና አንድነት በመላው ዓለም በምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፀሎት እና ምህላ ወስኗል። ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ፣ ጌዴኦ አማሮና ቡርጂ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ፥ ቋሚ ሲኖዶሱ 5ቱን የጳጉሜ ቀናት በፀሎትና ምህላ እንዲታሰብ መወሰኑን ገልፀዋል።…
"...ቋሚ ሲኖዶስ በወሰነው መሰረት ህዝበ ክርስቲያኑ #በአንድነት እና #በፍቅር ሊፀልይ ይገባል" - ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር)

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ፅ/ቤት የውጭ ጉዳይ መምሪያ የበላይ ኃላፊና የድሬዳዋና ጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶክተር) ፥ ቋሚ ሲኖዶስ በወሰነው ውሳኔ መሰረት ከጳጉሜ 1 እስከ 5 ድረስ ባሉት ቀናት በአንድነት እና በፍቅር መፀለይ እንደሚገባ ገልፀዋል።

"ምዕመናኑ በአምስቱ ዕለታት #ስለሀገር ሰላም፣ #ፍቅር እና #አንድነት፣ በፀሎት እና በምዕላ በትጋት ጊዜውን እንዲያሳልፍ ጥብቅ መመሪያ የተላለፈ መሆኑን በቋሚ ሲኖዶስ በኩል ለየአብያተክርስቲያናቱ እና ገዳማቱ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ላሉ ሁሉ እነዚህን ዕለታት በፀሎት እና በምዕላ እንዲያሳልፍ ተወስኗል" ሲሉ ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶክተር) ለEOTC ቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
ድሬ❤️

"ተዋዶ ያለበት እስላም ክርስቲያኑ
ከቶ አይዘነጋም ድሬ ላይ መሆኑ! "

በድሬዳዋ ሁሌም ቢሆን የነዋሪዎቿ #ፍቅር#አንድነት እና #አብሮነት ብሎም አሁናዊ የከተማዋ ሰላም ለሌሎች ምሳሌና ማሳያ ነው መባሉ በምክንያት ነው።

በጥምቀት ከተራ በዓል የእስልምና እምነት ተከታይ የሆኑ ወንድምና እህቶች በቀፊራ ፣ በለገሀሬ ፣ ኮኔል ፣ በድልድይ መጋላ እና በሌሎችም አካባቢዎች ለህዝበ ምእመኑ ውሀ፣ ኩኪሲችና ጣፍጭ ምግቦችን በማቅረብ እንኳን አደረሳችሁ ሲሉ ወንድማዊና ቤተሰባዊ ፍቅራቸውን ገልፀዋል።

ፎቶ ፦ ድሬ ፖሊስ ሚዲያ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia #US የማይክ ሐመር ስለ ኢትዮጵያ ቆይታቸው ምን አሉ ? አሜሪካ የኢትዮጵያን #ሉዓላዊነቷን እና #የግዛት_አንድነቷን_በማክበር ኢትዮጵያን ለመደገፍ ያላትን ፍላጎት እንደሚያረጋገጡ የሀገራቸውን አቋም ገልፀዋል። በአሜሪካ ህዝብ ለጋስነት ሀገሪቱ ለተቸገሩ ኢትዮጵያውያን ሰብዓዊ ድጋፍ እያደረገች መሆኑን አመልክተዋል። ሰላምን በማረጋገጥ በኩል የጋራ ፍላጎቶችን በሚመለከቱ ጉዳዮች ዙሪያ ከመንግስት…
#USA

በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩት የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር በድጋሚ ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ ተብሏል።

ልዩ መልዕክተኛው ከነገ ጀምሮ ወደ እስከ መስከረም 5 /2015 ኢትዮጵያ እና ወደ ቀጠናው ሀገራት እንደሚጓዙ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አሳውቋል።

በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ዳግም ያገረሸው ግጭት እንዲቆም እና የሰላም ንግግር እንዲጀመር ግፊት ያደርጋሉ ተብሏል።

አምባሳደር ሐመር በኢትዮጵያ ቆይታቸው የኢትዮጵያ መንግስት እና የአፍሪካ ህብረት ባለስልጣናትን ያነጋግራሉ።

በተጨማሪ የተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎችን ከሚወክሉ የሲቪል ማህበራት እና የፖለቲካ ተዋናዮች ጋር በመገናኘት በኢትዮጵያ ውስጥ ለሁሉም ህዝብ ዘላቂ ሰላም፣ ደህንነት እና ብልፅግና ለማምጣት የሚደረገውን ጥረት እንዴት በተሻለ ሁኔታ ማጎልበት እንደሚቻል ይወያያሉ።

አሜሪካ ለኢትዮጵያ #አንድነት#ሉዓላዊነት እና #ለግዛት_አንድነት ቁርጠኛ ነኝ ስትል በድጋሚ አረጋግጣለች።

አምባሳደር ሐመር ከሳምንታት በፊት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው አዲስ አበባ እና መቐለ ላይ ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት እና ህወሓት አመራሮች ጋር መወያየታቸው ይታወሳል።

በሌላ በኩል ፤ አሜሪካ ህወሓት /TPLF/ ከትግራይ ውጭ እየፈፀመ ያለውን ጥቃት ፤ የኢትዮጵያ መንግስትን የአየር ጥቃት እና የኤርትራን ዳግም ወደ ግጭት መግባቷን እንደምታወግዝ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ አንቶኒ ብሊንከን በኩል አሳውቃለች።

ሁሉም ወገኖች ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን በአስቸኳይ እንዲያቆሙ እና በሰላም ንግግር ላይ ለመሳተፍ የሚደረገውን ጥረት እንዲያጠናክሩ ጠይቃለች።

Via US Embassy AA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
* Update

የአሜሪካው የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር ከኢትዮጵያ ምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ጋር መነጋገራቸውን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አሳውቋል።

ሐመር በዚሁ ወቅት ጦርነት በአስቸኳይ ቆሞ ፤ በአፍሪካ ህብረት (AU) መሪነት ወደ ሰላም ድርድር ማምራት እንደሚያስፈልግ መወያየታቸውን መስሪያ ቤቱ ገልጿል።

ሐመር ከህወሓት ሊቀመምበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋር እንዴት/በምን ተገናኝተው እንደተነጋገሩ ባይገለፅም ለእሳቸውም ጦርነት በአስቸኳይ ቆሞ በአፍሪካ ህብረት መሪነት ወደ ሰላም ድርድር ማምራት እንደሚያስፈልግ እንዳስገነዘቧቸው ተገልጿል።

እንደ አሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለውን ግጭት ለማስቆም እና ወደ ድርድር ለመግባት በመጪዎቹ ቀናት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ፀሀፊ ሞሊ ፊ ፣ አምባሳደር ማይክ ሀመር እና ሌሎችም የአሜሪካ ዲፕሎማቶች ከአፍሪካ ህብረት እንዲሁም ከቀጠናው ቀልፍ ናቸው ከሚባሉት ተዋናዮች ተመድ ፣ አውሮፓ ህብረት ፣ ከዩናይትድ ኪንግደም ልዑካን ጋር ይመክራሉ።

መስሪያ ቤቱ ፤ የአሜሪካ ዓላማ በኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት መካከል ያለው ግጭት በአስቸኳይ እንዲቆም ፤ ኤርትራም ወደ ድንበሯ እንድትመለስ ዴፕሎማሲያዊ ግፊት ማድረግ ነው ብሏል።

ለግጭቱ ምንም አይነት ወታደራዊ መፍትሄ የለውም ያለው የአሜሪካ መንግስት መፍትሄድ በሁሉም ወገን ዘንድ የሰላም ድርድር ማድረግ ብቻ ነው ብሏል።

አሜሪካ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ለኢትዮጵያ #አንድነት#ሉዓላዊነት#የግዛት_አንድነት ቁርጠኛ አቋም አለኝ ስትልም በድጋሚ ማረጋገጧን ቪኦኤ ሬድዮ ዘግቧል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UpdateAU #ETHIOPIA የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት ፤ የትግራይ ክልል መንግስት ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያለውን ቁርጠኝነት እንዲሁም በአፍሪካ ህብረት መሪነት በሚካሄደው የሰላም ሂደት ውስጥ ለመሳተፍ ፍቃደኝነቱን መግለፁን በደስታ እንደሚቀበሉት ገልፀዋል። ይህን የገለፁት የትግራይ ክልልን እያስተዳደረ ያለው ህወሓት በአፍሪካ ህብረት መሪነት ከፌዴራል መንግስት…
#USA #ETHIOPIA

" አሜሪካ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ትቆማለች ፤ የአፍሪካ ህብረትን (AU) ዲፕሎማሲያዊ ጥረትን ትደግፋለች " - አንቶኒ ብሊንከን

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ሀገራቸው አሜሪካ #ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር እንደምትቆም እና በአፍሪካ ህብረት እየተመራ ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት #እንደምትደግፍ ገልፀዋል።

ይህን የገለፁት ለሊት ባወጡት መግለጫ ነው።

ብሊንከን ፤ የአፍሪካ ህብረት እየተካሄደ ላለው ግጭት ሰላማዊ መፍትሄ ለማበጀት የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት (TPLF) በተቻለ ፍጥነት ወደ ውይይት እንዲመጡ ለማድረግ እየሰራ ላለው ስራ ምስጋና አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ለሰላም ሲባል ከህወሓት ጋር " በየትኛውም ስፍራ፣ በማንኛውም ጊዜ "  ለመነጋገር ዝግጁ መሆኑን እንደገለፀ ያስታወሱት ብሊንከን ለዚህ የመንግስት ዝግጁነት የሚሰጥ ምላሽን እናበረታታለን ብለዋል። ህወሓት (TPLF) ግጭት ለማቆም እና ችግሮችን በውይይት ለመፍታት ያወጣውን መግለጫ እናበረታታለን ሲሉም አክለዋል።

ዓለም አቀፍ አጋሮች የሰላም ሂደቱን ለማገዝ ዝግጁ ናቸውም ብለዋል።

ኤርትራ እና ሌሎችም ግጭቱን ማቀጣጠል ማቆም አለባቸውም ሲሉ ገልፀዋል።

አሜሪካ የኢትዮጵያን #አንድነት#ሉዓላዊነት እና #የግዛት_አንድነት እንደምትደግፍ የገለፁት አንቶኒ ብሊንከን አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር ወደ #ጠንካራ_አጋርነት መመለስ ትፈልጋለች ሲሉ ገልፀዋል።

" የአዲስ ዓመት መንፈስን ታሳቢ በማድረግ የአገሪቱ መሪዎች አገሪቱ መከራዋ ወደሚያበቃበት እና ዘላቂ ሰላም ሊያስገኝ ወደሚያስችል መንገድ እንደሚሯት ጥሪ እናቀርባለን " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA #ETHIOPIA " አሜሪካ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ትቆማለች ፤ የአፍሪካ ህብረትን (AU) ዲፕሎማሲያዊ ጥረትን ትደግፋለች " - አንቶኒ ብሊንከን የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ሀገራቸው አሜሪካ #ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር እንደምትቆም እና በአፍሪካ ህብረት እየተመራ ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት #እንደምትደግፍ ገልፀዋል። ይህን የገለፁት ለሊት ባወጡት መግለጫ ነው። ብሊንከን ፤…
#USA #ETHIOPIA

" ለኢትዮጵያ አንድነት ፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ቁርጠኛ ነን " - አሜሪካ

አሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛዋ አምባሳደር ማይክ ሀመር ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች፣ ከአፍሪካ ህብረት እና ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር #ውጤታማ ውይይት አድርገዋል ስትል አሳወቀች።

ሀገሪቱ ይህን ያሳወቀችው ዛሬ አዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲው በኩል ነው።

የአምባሳደር ማይክ ሐመር የኢትዮጵያ ጉብኝት ውጤታ ነበር ያለችው አሜሪካ  " ለኢትዮጵያ #አንድነት#ሉዓላዊነት እና #የግዛት_አንድነት ቁርጠኛ ነን " ስትል አስታውቃለች።

በተጨማሪ ሁሉም ኢትዮጵያውያን እንዲበለጽጉ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ እንደምትፈልግ ገልፃለች።

@tikvahethiopia