TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#የፀጥታ_ጉዳይ " የክልል እና የፌደራል የጸጥታ ሀይል እንዲገባልን አመልክተናል " - አቶ ውብሸት አበራ ታጣቂዎች በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ከሌሊት 8 ሰዓት ጀምሮ ተኩስ እንደከፈቱ ተሰምቷል። ለአል ዓይን ኒውስ የደራ ወረዳ፤ ጉንዶ መስቀል ከተማ ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው ፤ መንግስት በአሸባሪነት የፈረጀው የኦነግ ሸኔ ቡድን ታጣቂዎች ወደ ከተማዋ ዘልቀው በመግባት ከባድ…
#ትኩረት

በሰሜን ሸዋ ፤ ደራ ወረዳ ያለው ሁኔታ ከፍተኛ ትኩረት እንደሚያስፈልገው በወረዳው ቤተሰቦቻቸው የሚኖሩ የቲክቫህ አባላት አመልክተዋል።

" ንፁሃን በጭንቀት ውስጥ ነው ያሉት " ሲሉ የገለፁት የቤተሰብ አባላቶቻችን ዛሬ በጉንዶ መስቀል ከተማ ከፍተኛ የሆነ የተኩስ እሩምታ ሲሰማ እንደነበር እና ነዋሪውም #ለደህንነቱ_በመስጋት በየቤቱ ተቀምጦ እንደነበር ተናግረዋል።

በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ #ጉዳት መድረሱን አመልክተው አፋጣኝ እንዲሁም አስተማማኝ መፍትሄ እንዲፈልግ ድምፃቸውን አሰምተዋል።

የደራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ውብሸት አበራ ዛሬ ለአል ዓይን ኒውስ በሰጡት ቃል ፤ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ወደ ደራ ወረዳ ዋና ከተማ ጉንዶ መስቀል መግባታቸውን ገልፀዋል።

ከጠዋት ጀምሮ በከተማዋ ባሉ ባንኮች፣ የመንግስት ተቋማት እና የግለሰቦች ንብረት ላይ ዘረፋ ሲፈፀም እንደነበር ጠቁመው ወረዳው የክልል እና የፌደራል የጸጥታ ሀይል እንዲገባለት ማመልከቱን አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia