TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ትላንት በትራፊክ አደጋ ከ15 በላይ ሰዎች ህይወት ማለፉን ተዘግቦ ነበር፦

• ከሟቾቹ ውስጥ ሦስቱ ጓደኛማቾች ይገኙበታል
• 3ቱም የ3ኛ ዓመት የአርኪዮሎጂ ተማሪዎች ናቸው
• ያቤሎ በሀዘን ተመታለች!
• እንደወጣን አንመለስም! …

በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን ያቤሎ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ ከ15 በላይ ሰዎች ህይወት አልፏል።

አደጋው የተከሰተው ከኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ያቤሎ ከተማ ወደ ደቡብ ክልል ኮንሶ ከተማ ኮንትሮባንድ ጭኖ በፍጥነት ሲጓዝ የነበረ ተሽርካሪ ከከባድ የጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው።

በደረሰው ከባድ የትራፊክ አደጋ ከ15 ሰዎች በላይ ህይወት አልፏል። ከቦራና ወደ #ወላይታ_ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ለ2ኛ ሴምስተር ምዝገባ ሲጓዙ የነበሩት የ3ኛ ዓመት የ#አርኪዮሎጂ #archeology ተማሪዎች የሆኑት ተማሪ #መቅደስ_ተሰፋዬ፣ ተማሪ #ትዝታ_ይድነቃቸው እና ተማሪ #ከና_ሚፊታ በመኪና አደጋ ሕይዋታቸው ተነጥቋል፡፡

ከሟቾቹ ውስጥ ከላይ በፎቶው የምትመለከቷቸው ሦስት ጓደኛሞች የአደጋው ሰለባ ሆነዋል፡፡ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የዘንድሮ #ተመራቂ ተማሪዎች ነበሩ::

• (በመንገድ ላይ እየቀረን ነው)

ያገሬ ልጆች እንደወጡ አይመለሱም፤ አንመለስም!

ነፍስ ይማር!

Via Getu Temsegen
@tsegabwolde @tikvahethiopia