TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጀግኒት

ተማሪ DAGMAWIT BEDELU #በዘንድሮው የዩኒቨርሲቲ/የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና 631 ያስመዘገበች ጀግኒት! #ኢትዮጵያዊት

#631 #ባህርዳር #SOS

🗓የሌሎች #ጀግኒቶች ውጤት ይቀጥላል🔄
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#SOS

"ኤስ ኦ ኤስ የህፃናት መንደሮች በኢትዮጵያ" የተሰኘው ድርጅት ከሰሞኑን የ50ኛ ዓመት በዓሉን አክብሮ ነበር።

በዚህም ወቅት ፤ ድርጅቱ በአጠቃላይ፦
- በአማራጭ የቤተሰብ ክብካቤ -በቤተሰብና ማህበረሰብ አቅም ግንባታ
- በአስቸኳይ ጊዜ ሰብዓዊ ድጋፍ በትምህርት
- ጤና እና በወጣቶች ማብቂያ ፕሮግራሞች ከ8.1 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎችን እንደደረሰ ገልጿል።

እንዲሁም በእነዚሁ ፕሮግራሞች መሠረት በዚህ ዓመት 700 ሺሕ አካላትን ለመድረስ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።

በጦርነት፣ በድርቅ እና መሰል ክስተቶች ወላጆቻቸውን ያጡ ልጆችን ራሳቸውን እንዲችሉ እርዳታ ማድረግ ዋነኛ ዓላመው መሆኑን የገለጸው ድርጅቱ በኢትዮጵያ በ9 ክልሎች እየሰራ ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦

° በተለያዩ ክልሎች በተካሄዱት ጦርነቶችና እየተካሄዱ ባሉ ግጭቶች ድርጅቱ ምን ያህል ወላጅ አልባ ህፃናትን አገኘ ?

° በአዲስ አበባ ከተማ ጎዳና ላይ ለሚተዳደሩ ወላጅ አልባ በርካታ ልጆን ለመርዳት ምን እየሰራ ? ነው ሲል ጥያቄ አቅርቧል።

ምክትል ብሔራዊ ዳይሬክተር ኤቢሳ ጃለታ ቁጥቸውን ለመግለጽ ቢታቀቡም በጦርነት ወላጆቻቸውን ያጡ ህፃናትን በጎረቤት፣ በቅርብ ቤተሰቦቻቸው አስጠግቶ እየረዳ መሆኑን ተገናግረዋል።

አ/አ የሚገኙትን በተመለከተም ፕሮጀክት በመቅረጽ እየሰራ መሆኑንን አስረድተዋል።

ኤስ ኦ ኤስ የህፃናት መንደሮች በኢትዮጵያ ከ1949 ዓ/ም ጀምሮ የቤተሰብ እንክብካቤ ላጡ ህፃናት በፍቅር የተሞላ ቤተሰብ ሲሰጥ የቆየው የዓለም አቀፉ የኤስ ኦ ኤስ ፌደሬሽን አካል ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@TikvahEthiopia