TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
* Amhara "በወሎ ሕዝብ ላይ ያንዣበበው አደጋ ታሪክ ራሱን እንዳይደግም ያስፈራል " - እናት ፓርቲ እናት ፓርቲ በወሎ ጉዳይ መግለጫ አውጥቷል። ፓርቲው በላከልን መግለጫ ፥ በወሎ አካባቢ ያንዣበበው አደጋ እጅጉን እንደሚያሳስበው ገልፆ አፋጣኝ መፍትሔ ያሻዋል ብሏል። እናት ፓርቲ የወሎ ህዝብ ላለፉት ዓመታት በማንነቱ ምክንያት ግፍ ተፈፅሞበታል ያለ ሲሆን ያለፈው መከራና ሰቆቃ አልበቃ ብሎ ሽብረተኛ…
#Wollo / #ወሎ : እናት ፓርቲ በመግለጫው ፦

1. መንግስትን ፦

የትኛውም ዋጋ ተከፍሎ የወሎ እና የአካባቢውን ማኅበረሰብ ከህወሓት ቡድን ነጻ እንዲያወጣ ጠይቋል።

2. መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ የእርዳታ ድርጅቶችን ፡-

በአካባቢው ያለውን ሰቆቃ በሚመጥን መልኩ እጃቸውን ዘርግተው ቢያንስ የነዋሪውን ረሃብ እንድታስታግሱለት፣ በእቅፉ ያሉና የጣር ድምጽ የሚያሰሙ ሕጻናት ልጆቹ ድምጽ ተሰምቷቸው በአፋጣኝ እንዲደርሱላቸው ተማጽኗል።

3. ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ፡-

በሩቅ የሰማነው የረሃብ እልቂት በወሎ ሕዝብ ላይ አንዣቧልና ለነገ ሳይ ከጉርሱ እየቀነስክ ወሎን እንዲታደግ ፤ ችግሩን አርቆ መመልከት ከተቻለ እንደሀገር የሚገባበት ቀውስ ከባድ ስለሆነ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንደየአቅሙ እንዲረባረብ ጥሪ አቅርቧል።

4. ለፖለቲካ ፓርቲዎች ፡-

እስከአሁን ሲደረግ እንደቆየነው ሁሉ " በትብብር የወሎ ሕዝብ ድምጽ እንሁን ብሎም የአቅማችንን እንድናደርግ " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

5. መገናኛ ብዙኃንን ፡-

የረሃብ አደጋ ላንዣበበበት የ #ወሎ_ሕዝብ_ድምጽ እንዲሆኑ ጠይቋል። አሁን ያለው ሁኔታ ቢሸፋፈንም እንዲህ ያለው ሽል ገፍቶ መውጣቱ ስለማይቀር ያኔ በታሪክ ፊት አንገትን ከመድፋት አሁን ረሃብ ላንዣበበት የወሎ ህዝብ ድምፅ እንዲያሰሙ ጠይቋል።

@tikvahethiopia