TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ከፍተኛ_ጥንቃቄ_አዲስ_አበባ😷

በየዕለቱ ከፍተኛው የኮቪድ-19 ሞት ሪፖርት እየተደረገ የሚገኘው ከአዲስ አበባ ከተማ ነው።

ለአብነትም ፦

- ዛሬ የካቲት 11 በሀገር አቀፍ ደረጃ ሪፖርት ከተደረገው የ12 ሰዎች ሞት ፤ 11ዱ ሰዎች ከአዲስ አበባ ናቸው።

- የትላንት ሪፖርት የከተማው አስተዳደር ጤና ቢሮው አላሰራጨም።

- የካቲት 9 በሀገር አቀፍ ደረጃ ከተመዘገበው 14 ሞት 12ቱ ሰዎች ከአዲስ አበባ ናቸው።

- የካቲት 8 በሀገር አቀፍ ደረጃ ከተመዘገበው 15 ሞት 11ዱ ሰዎች ከአዲስ አበባ ናቸው።

በየዕለቱ የሟቾች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል። እጅግ በርካታ ሰዎችም በፅኑ ታመዋል ፤ በርካቶችም የመተንፈሻ መሳሪያ ማግኘት ባለመቻላቸው ከፍተኛ ስቃይ እያጋጠማቸው/ህይወታቸውንም እያጡ ነው።

ውድ አባላት በየትኛውም አይነት ሁኔታ ውስጥ ብትሆኑ ሳትዘናጉ እራሳችሁን እና ቤተሰቦቻችሁን ከዚህ አስከፊ ወረርሽኝ እንድትጠብቁልን አደራ እንላለን።

#Purpose #TikvahFamily

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia