TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ለኩ⬆️

በለኩ ከተማ በ"እኔም ለወገኔ ወጣቶች" አስተባባሪነት ትላንት በጁኒየር ትምህርት ቤት የተጀመረው የደም ልገሳ በዛሬው ዕለት በለኩ #ሆስፒታል መቀጠሉን ሰምተናል። "ከስጦታዎች ሁሉ የላቀ ውዱ ስጦታ #የደም ስጦታ ነው" በሚል መሪ ቃል ነው የድም ልገሳው እየተደረገ የሚገኘው።

#ደም_በመገስ_ተደምረናል!

©Devila
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሁሉም ውስጡ #ስጋና #ደም
ቀለም መልኩ ቢለያይም
ወላጁ #አንድ ነው አባቱ አንድ ነው
ዞሮ ዞሮ #አዳም
.
.
ሰውነት ይከበር!
ሰውነት ይቅደም!
#ETHOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሁሉም ውስጡ #ስጋና #ደም
ቀለም መልኩ ቢለያይም
ወላጁ #አንድ ነው አባቱ አንድ ነው
ዞሮ ዞሮ #አዳም
.
.
ሰውነት ይከበር!
ሰውነት ይቅደም!
#ETHOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አማራ 🕊 ቅማንት!

‹‹ድርጅት እና መሪዎች ያልፋሉ ህዝብና #ታሪክ ግን ይቀጥላል፤ የምናልፍ መሪዎች #የማያልፍ ጠባሳ ጥለን እንዳናልፍ ልንጠነቀቅ ይገባል፡፡››

‹‹ማንነትን ማክበር እና ማስከበር ስንል አጥር ማጠር እና የልዩነት ግንብ መገንባት ማለት አይደለም ፡፡ህዝብን ማድመጥ እና ታሪካዊ ወሰኑን ማስከበር እንጅ ተመልሶ ያደረ ጥያቄ ነው እያሉ ማለፍ ታሪኩ ያለፈበት ሂደት ነው፡፡››

‹‹ልታከብረን እና ልናከብራት የምንችላት ሃገር ለመገንባት በመጀመሪያ በህግ የበላይነት ልንገዛ ይገባል፡፡›› ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን
.
.
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ #ደመቀ_መኮንን ግጭት ለታላቅ ሃገር እና ተስፋ ለሰነቀ ህዝብ የሚመጥን አይደለም፤ እንዲህ አይነት ህዝብን ከህዝብ የማጋጨት ስራ ዛሬ ሳይሆን በሁለተኛው የጣሊያን ወረራ ወቅት አማራን የትኩረት ማዕከል አድርጎ ሲሰራበት ነበር ዳሩ የህዝቡን አንድንነት #ማፍረስ አልተቻላቸውም እንጅ ብለዋል፡፡

አማራን ከአገው፣ ቤተ እስራኤላዊያንን ከአማራ እንዲሁም ቅማንትን ከአማራ ለማጋጨት ጥረት ተደርጎ ነበር፤ ነገር ግን አባቶቻችን በብልጠት ሴራውን አክሽፈው እልፍ ዘመን የዘለቀ አብሮነትን አውርሰውናል ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡

ማንነትን ማክበር እና ማስከበር ስንል አጥር ማጠር እና የልዩነት ግንብ መገንባት ማለት አይደለም ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህዝብን ማድመጥ እና ታሪካዊ ወሰኑን ማስከበር እንጅ ተመልሶ ያደረ ጥያቄ ነው እያሉ ማለፍ ታሪኩ ያለፈበት ሂደት ነው ብለዋል፡፡

ልታከብረን እና ልናከብራት የምንችላት ሃገር ለመገንባት በመጀመሪያ በህግ የበላይነት #ልንገዛ ይገባል፡፡ ሃገራችን ያከበረችንን ያክል አላከበርናትም ያሉት አቶ ደመቀ ሃገር ግንባታ ጊዜ ይወስዳልና በትዕግስት ሃገር ልንገነባ ይገባል ብለዋል፡፡

እኛ እና እናንተ አሉ አቶ ደመቀ ‹‹እኛ እና እናንተ ከግለሰብ እልፍ ያለ ኃላፊነት ስላለብን ስሜት ሳይገዛን እና ከንፈራችን እየመጠጥን እንዳናዳማ ትክክለኛ መሪ እና መፍትሄ ፈላጊዎች ልንሆን ይገባል ብለዋል፡፡››

ይህ ህዝብ አብሮ ኖሯል ፤ ተዋልዷል ፤ #ደም አስተሳስሮታል እና! ይህ ቀን አልፎ ነገ አብሮ መኖሩ ስለማይቀር ‹‹መሪና ድርጅት ያልፋሉ ህዝብና ታሪክ ግን በዘመናት መካከል ይቀጥላሉና በሚያልፍ የመሪነት ዘመናችን የማያልፍ የታሪክ ጠባሳ እንዳንተው ልንጠነቀቅ ይገባል››
ብለዋል፡፡

🔹በጎንደር ከተማ እየተካሄደ ያለው የሰላም መድረክ እንደቀጠለ ነው፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የጤናማ እናትነትን ወር ምክንያት በማድረግ የጤና ሚኒስቴር የዋናው መ/ቤት ሠራተኞች በዛሬው ዕለት #ደም_ለገሡ፡፡ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተኘው መረጃ እንደሚያመላክተው የጤና ሚኒስቴር ዴኤታዋ ወ/ሮ #ሰሀረላ_አብዱላሂ ደም በለገሱበት ውቅት ባደረጉት ንግግር ይህ የደም መለገስ ኘሮግራም ሀገራዊ ጠቀሜታው እጅግ የጎላ በመሆኑ ሌሎች ሴክተር መ ቤቶችም ይህንኑ ፈለግ በመከተል ደም እንዲለግሱ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከወር በፊት ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲበር #ለተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር 302 ተጓዥ ለነበሩ እና ሕይወታቸው ላለፉ ሰዎች የ40 ቀን ማስታወሻ በጋራ ተከናወነ። የዝክር ስነ-ሥርዓቱ፦የሟቾች ቤተሰቦች፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት፣ የቢሾፍቱ ወጣቶች እና የቱሉ ፈርዳ ወረዳ የሃማ ቁንጡሽሌ ቀበሌ ነዋሪዎች እንዲሁም የተለያዩ የእምነት አባቶች በተገኙበት ጧፍ በማብራት እና በጸሎት ተከናውኗል። አደጋው በደረሰበት የሃማ ቁንጥሽሌ አከባቢ በአደጋው ሕይወታቸውን ላጡ መታሠቢያ እንዲሠራ ነዋሪዎቹ ጠይቀዋል። በዕለቱም 2500 የሚሆኑ #የቢሾፍቱ ወጣቶች በአደጋው ስፍራ #ደም ለግሰዋል።

Via DW
ፎቶ፦ TIKVAH-ETHIOPIA(DakStar)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እሁድ እንዴት እያለፈ ነው?

"እኛ የፖይለት ወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር ከቢሾፍቱ ወጣቶች ጋር በመተባበር በየአመቱ የምናዘጋጀው የደም ልገሳ ፕሮግራም ዘንድሮም ቀጥሎ ዛሬ እሁዳችንን #ደም_በመለገስ እና ሌሎችም እንዲለግሱ እያስተባበርን እንገኛለን።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሁሉም ውስጡ #ስጋና #ደም
ቀለም መልኩ ቢለያይም
ወላጁ #አንድ ነው አባቱ አንድ ነው
ዞሮ ዞሮ #አዳም
.
.
ሰውነት ይከበር!
ሰውነት ይቅደም!
#ETHOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የባሕር በር ጉዳይ የቅንጦት ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው " - ኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ምን አሉ ? " ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት የቅንጦት ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። ከሶማሌላንድ ጋር የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ ከዓላማው ውጪ የሆኑ የተሳሳቱ መረጃዎች ተሰራጭተዋል። የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የቅንጦት ሳይሆን…
#ኢትዮጵያ🇪🇹

" ... ለሶማሊያ በችግር ጊዜ ብዙ ድጋፍ ያላደረጉ #አንዳንድ_ተዋናዮች ራሳቸውን እንደ እውነተኛ ወዳጆቿ አድርገው ለማሳየት እየሞከሩ ነው " - አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ምን አሉ ?

- ኢትዮጵያ ለሶማሊያ #ሰላም እና #ደህንነት ያላትን ቁርጠኝነት በውድ ልጆቿ #ደም እና #ላብ በግልፅ አሳይታለች።

- ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ድንበር ተጋርተው የሚኖሩ ጎረቤቶች ብቻ ሳይሆኑ የጋራ የሆነ ቋንቋ፣ ባህል እና ህዝብ የሚጋሩ ወንድማማች ሀገራት ናቸው።

- ኢትዮጵያ እና ሶማሊያን የሚያስተሳስሩ ጉዳዮች ጠንካራ ናቸው ፤ እጣ ፈንታችን የማይነጣጠል ነው።

- ከሶማሌላንድ ጋር የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ለኢትዮጵያ የንግድ ግንኙነት የሚሆን የባህር አገልግሎት የሚሰጥ የትብብር እና አጋርነት ስምምነት ነው። ስምምነቱ በየትኛውም ሀገር ላይ ሉዓላዊነትን የሚጥስ / የሚገዳደር / በግዳጅ የየትኛውንም ሀገር ሉዓላዊነት የሚረግጥ አይደለም።

- እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ለሶማሊያ በችግር ጊዜ ብዙ ድጋፍ ያላደረጉ አንዳንድ ተዋናዮች ራሳቸውን እንደ እውነተኛ ወዳጆቿ ለማሳየት እየሞከሩ ነው። ለዚህ ደግሞ ያነሳሳቸው ለሶማሊያ ያላቸው ወዳጅነት ሳይሆን #ለኢትዮጵያ_ያላቸው_ጥላቻ / የጠላትነት ስሜት መሆኑ ግልጽ ነው።

- እነዚህ ተዋናዮች አጀንዳቸው የአፍሪካ ቀንድ ሰላም ፣ መረጋጋት እና ደህንነት አይደለም። ሊዘሩ የፈለጉት #አለመግባባት እና #ትርምስን ነው። እየታየ ያለው ነገር ውጥረት የሚያባብስ እንዲሁም ደግሞ አጋጣሚውን ለመጠቀም ለሚፈልጉ የውጭ ተዋናዮች ፍላጎት ብቻ የሚያገለግል ነው።

- ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመስረተ ሁሉን አቀፍ ቀጠናዊ ትስስርን ለመፍጠር ከሁሉም ጎረቤቶቿ ጋር በትብብር መንፈስ ለመስራት እየጣረች ነው።

- ኢትዮጵያ ውጥረትን ከሚፈጥሩና ከሚያባብሱ መግለጫዎች፣ ንግግሮች እና ትርክቶች ይልቅ ቀጣይነት ያለው ውይይት ማድረግ የተሻለ አማራጭ እንደሆነ በጽኑ ታምናለች።

#AmbassadorRedwanHussien #X

@tikvahethiopia