TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
“ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ መንግሥት ነው፣ ያለው #እኔ የምመራው መንግሥት። አንድ ዓመት ተኩል በኋላ እኔ እና ድርጅቴን ካልመረጣችሁ አቅፌ ስሜ እሰጣችኋለሁ። ከምርጫ በፊት በ 3 ወር በ 5 ወር መንግሥት እሆናለሁ የሚል #ቅዠት ኢትዮጵያ ውስጥ #አይሰራም። ይሄ ቅዠት የማይሰራበት ምክንያት እኔ እንኳን ብፈቅድ አንድ ዓመት ተኩል ታግሶ ማሸነፍ ያልቻለ ፓርቲ ነገ መጥቶ እዚህ ቢገባ ያምሰናል እንጂ እንዴት ይመራናል? 30 ዓመት 20 ዓመት የኢትዮጵያን ምድር መርግጥ ያልቻሉ ሰዎች ይብቃ ብለን ሕግ ቀይረን፣ ባሉበት አናግረን፣ ለምነን አምጥተን ስናበቃ #ልንወጋ አይገባም” ጠ/ሚ #ዐብይ_አሕመድ (ዶ/ር)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH የተሰሩ ተግባራት!

√2007 ዓም--ከዛሬዎቹ ቤተሰቦች 600 መፅሃፍትን በማሰባሰብ በሃዋሳ ከተማ ለሚገኝ ላይብረሪ ድጋፍ አድርጓል/መፅሃፉ የተሰባሰበው ከተማሪዎች እና ሰራተኞች ነው/

√2007 ዓም -- ሀዋሳ ከተማ በተዘጋጀ ልዩ የበጎ አድራጎት እና የጥበብ ፌስቲቫል የተገኘ 5,000 ብር ለአረጋዊያን ድጋፍ ተደርጓል።/ብሩ የተገኘው በተዘጋጀው ልዩ ዝግጅት ላይ ከተገኙ ሰዎች ነበር በወቅቱ መግቢያው 15 ብር ነበር/ በተጨማሪ ሜሪጆይ ለሚገኙ አረጋዊያን የአልባሳት ድጋፍ ለማድረግ ተሞክሯል።

√2008 ዓም--በተመሳሳይ 400 መፅሃፍትን በማሰባሰብ ድጋፍ ተደርጓል። እንዲሁም የመማር አቅም ለሌላቸው 25 ተማሪዎች የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ ተችሏል/ድጋፍ የተደረገው በወቅቱ ልዩ የኪነ ጥበብ ዝግጅት በማዘጋጀት በተገኘ ገቢ ነው/

√2009 ዓም--በተመሳሳይ ከ300 በላይ የመማሪያ መፅሃፍትን በማሰባሰብ ገቢ ማድረግ ተችሏል። በውቅቱ ለአዲስ አመት ዋዜማ በተዘጋጀ ዝግጅት እንዲሁም ከተለያዩ ድርጅቶች እየዞረ በተሰበሰበ የትምህርት ቁሳቁስ የ30 ተማሪዎችን የትምህርት ወጪ መሸፈን ተችሏል።

√2010 ዓም--ከአለን ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ማህበር ጋር በመሆን 1000 መፅሃፍትን ለማሰባሰብ ተችሏል።

√2011 ዓም--በሀገሪቱ ያለውን ችግር እንዲፈታ ለማገዝ እና ወጣቶች ለሀገራቸው እንዲቆሙ የStopHateSpeech መድረኮችን እያዘጋጀ ይገኛል።

ከላይ ያሉት ጥቂት ስራዎች ናቸው👆

TIKVAH-ETH በቴሌግራም ከመጣ በኃላስ፦


√ወቅታዊ እና የተመረጡ መረጃዎችን ከየተኛውም ወገንተኝነት በፀዳ መልኩ እያደረሰ ይገኛል።

√ጥቆማዎችን ያደርሳል

√የተቸገሩ ወገኖችን ህይወት ለማትረፍ ይረባረባል።

√የታመሙትን ይጠይቃል።

√ጠንካራ ሀገር እንዲገነባ በገለልተኝነት የተለያዩ የአስተሳሰብ ማጎልበቻ ስራዎችን ይሰራል።

√ሰላም እና አንድነት ላይ ያተኮሩ ሀገር አቀፍ ስራዎችን ይሰራል።

በዚህ አጋጣሚ ለመግለፅ፦

TIKVAH-ETH ከየትኛውም የመንግስት እና የግል ተቋማት ጋር አብሮ #አይሰራም። መሪዎቹ የቤተሰቡ አባላት ናቸው። እስከዛሬ በማንም ተፅኖ ስር ያልወደቀ ነው። የገንዘብ ምንጩ የቻናሉ ማስታወቂያ ብቻና ብቻ ነው።

እስከዛሬም በተሰሩት ስራዎች፦ የትኛውም የመንግስት አካል #በገንዘብም #በሀሳብም የደገፈን #የለም። ሁሉም ስራ በቻናሉ አባላት የሚሰራ ብቻ ነው።

እኔም፦
√ከፖለቲካ ወግንተኝነት ነፃ ነኝ
√የየትኛውም ድርጅት አባልም ተከታይም አይደለሁም
√ከየትኛውም ድርጅት ጋር ትውውቅ የለኝም

አመሰግናለሁ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia