TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ክቡር አቶ #ገዱ_አንዳርጋቸው ግብፅ ናቸው...

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ክቡር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በግብፅ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ካይሮ ይገኛሉ፡፡ በጉብኝታቸውም ከግብፁ ፕሬዚደንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ጋር በሁለትዮሽ ግንኙነት ፣ በአካባቢያዊና በአለም አቀፋዊ የጋራ ጉዳዮች ላይ #መወያየታቸውን በግብፅ የኢትዮጵያ ኢምባሲ አመልክቷል። እንዲሁም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በካይሮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጽህፈት ቤት በመገኘት ከሰራተኞቹ ጋር ዉይይት አድርገዋል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሀምሌ 22 የሚካሄደውን #የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር መሠረት በማድረግ በሚሲዮኑ ጽህፈት ቤት የችግኝ ተከላ አካሂደዋል፡፡

Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia