TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
86,660 ብር ደርሰናል!

ምዕራፍ አንድ በ24 ሰዓት ውስጥ ሊጠናቀቅ ነው! 13,340 ብር ብቻ ይቅረናል(100,000 ብር)። የብሩን ማጠን ሳይሆን #አብሮነታችንን ማስመስከራችን ለቀጣይ ጉዟችን ትልቅ አቅም ይሆነናል። የዛሬው ህብረታችን ነገም ሌሎች ወገኖቻችን ለማገዝ ትልቅ አቅም ይፈጥርልናል።

#ኦሮሚያ #ሀረሪ #ደቡብ #ትግራይ #ሱማሌ #አፋር #ቤንሻንጉል #ጋምቤላ #አማራ #አዲስ_አበባ_ከተማ_አስተዳደር #ድሬዳዋ_ከተማ_አስተዳደር የምትገኙ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ትልቅ ክብር አለን!

Account number(CBE): 1000277462439

@tsegabwolde @tikvaethiopia
#አዲስ_አበባ_ከተማ_አስተዳደር

ባለዲግሪው መፃህፍት አዟሪ በብልሽት ለረጅም ጊዜ ቆሞ የነበረ ተሽከርካሪ ለስራ እንዲሆነው ከከተማ አስተዳደሩ ተበረከተለት!

ከተመረቀ በኋላ ለአራት አመታት መፃህፍት በማዞር ህይወቱን ሲመራ የነበረው ወጣት አንዷለም ይስሃቅ ከከተማ አስተዳደሩ ለረጅም ጊዜ ቆሞ የነበረ ተሽከርካሪ በኢ/ር ታከለ ኡማ ተበርክቶለታል።

ወጣቱ ደርሶበት በነበረው የአእምሮ ህመም ችግር ሳይበገር እና ስራ ጠባቂ ሳይሆን እራሱን ለመለወጥ ያደረገው ጥረት ለብዙዎች አርአያ የሚሆን እንደሆነም ተነግሯል።

በጥቂት ጊዚያት ውስጥም በከተማዋ ያለ አገልግሎት የቆሙ ሌሎች 700 የሚሆኑ አንበሳ የከተማ አውቶብሶችን ወደ ተንቀሳቃሽ ሱቆች በመቀየር በከተማዋ ለሚገኙ ስራ ፈላጊ ወጣቶች ለመስጠት ዝግጅቶች እየተደረጉ ይገኛሉ።

ይህ ተግባር በአንድ በኩል የከተማ አስተዳደሩ ለወጣቶች ስራ የመፍጠር ግዙፍ እቅድ አካል ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በችግሮች ሳይበገሩ ራሳቸውን ለመቀየር እየሞከሩ ያሉ ወጣቶችን ለማበረታታት አላማ ያደረገ ተግባር ነው።

Via #mayorofficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia