TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሻሸመኔ ዛሬ #በጥቂት ወጣቶች የተፈፀመው ድርጊት ልብ ሰባሪ ነው። ይህን መሰሉ ስርአት አልበኝነትን ህዝቡ ሊታገለው ይገባል። ህግ እያለ በምንም መልኩ ማንም ሰው ወይም ቡድን ፍርድ ሊሰጥ አይችልም። ወጣቱ ደሙን ያፈሰሰው እዚህም እዚያም ስርአት አልበኝነት እንዲፈጠር አይደለም። ዛሬ የተፈፀውን ዘግናኝ ድርጊት የፈፀሙ አካላት ለህግ እንዲቀርቡም እንጠይቃለን።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኦሮሚያ ክልል⬇️

በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች የሕግ የበላይነትን ለማስከበርና ሕገ ወጥነትን ለመከላከል በተሰራው ስራ የተለያዩ ሕጋዊ እርምጃዎች ተወስደዋል፡፡

#ሱሉልታ

በቄሮ ስም እንቅስቃሴ በማድረግ ሌሊት የግለሰቦችን ቤት በማፍረስና ቆርቆሮ በመውሰድ ላይ የተሰማሩ 4 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር
ውለዋል፡፡

#ሻሸመኔ

ባለፈው ሳምንት በከተማው የተፈጸመው ወንጀል እጃቸው አለበት ተብለው የተጠረጠሩ 7 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

#ቡራዩ

የቄሮ አመራር ነኝ በማለት መታወቂያ አዘጋጅቶ የተለያዩ ተቋማት በግድ ስፖንሰር እንዲያደርጉት ሲጠይቅ የነበረ፣ ቲተር: ማዕተምና የመታወቂያ ወረቀት በቄሮ ስም አዘጋጅቶ በመሸጥ ሲነግድ የነበረ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

#ለገጣፎ_ለገዳዲ

በቄሮ ስም የ62 ወጣቶችን ፎቶ በማሰባሰብና ወረቀት ላይ በመለጠፍ የቄሮ አደረጃጀት ከቀበሌ እስከ ላይ መኖር አለበት በሚል ወጣቶችን
ሲያታልሉና ሲያደረጁ የነበሩ 2 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

#ጅማ

በሕገ ወጥ ስራ ላይ ተሰማርተው ሕገ ወጥ ግንባታ ሲያካሄዱ የነበሩ 42 ሰዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 8 ሰዎች ላይ ሙሉ መረጃ ተሰባስቦ ለሕግ ሊቀርቡ ነው፡፡
ድንገት በተደረገው ፍተሻም 2ሽጉጥና 180 ጥይቶች ተይዘዋል፡፡

#አዳማ

በቅርቡ በከተማው ለተከሰተው ግጭት መነሻ በመሆን ሰዎችን ሲያነሳሱ የነበሩና ግጭቱ የብሔር መልክ እንዲይዝ አድርገዋል የተባሉ 8 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

#ሞጆ

ጨለማን ተገን በማድረግ ፋብሪካን ለመዝረፍ ሲንቀሳቁ የነበሩ 2 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ በአንደኛው ግለሰብ እጅ ሽጉጥ ተይዟል፡፡

#ሰበታ

በሕገ ወጥ ግንባታ ላይ የተሰማሩ፣ ምግብ ቤት ገብተው በመመገብ ሒሳብ የማይከፍሉና ተደራጅተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 14 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ምንጭ:- የኦሮሚያ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሻሸመኔ የወላቡ የወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል። WALDAA TOLA OOLTUMMAA DARGAGGOOTA WALAABUU
#ሻሸመኔ
#ሀዋሳ
#ነቀምት
#አሰላ
#አዲስአበባ
#ሽሬ
#ደብረብርሃን
#ወላይታሶዶ
#አርባምንጭ
#ጅግጅጋ
#አዳማ
#ድሬዳዋ
#ባህርዳር
#መቐለ
#ሀረር
#ጎንደር

ከሌሎች በርካታ ከተሞች ከሚገኙ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች የSAT ውጤት ያልጠበቁት እንደሆነ በመግለፅ ቅሬታቸው እያሰሙ ይገኛሉ። የሚመለከተው አካል ማብራሪያ እንዲሰጥበትም ጠይቀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ዶዶላ #ሻሸመኔ #ቡታጅራ #ጅማ #ከሚሴ

ኑ ትውልድ እንገንባ!

ቤት ካላችሁ የመማሪያ መፅሃፍ ቢያንስ አንዱን ለሀገራችሁ በስጦታ አበርክቱ!

#ዶዶላ
0920068173/ቶሎሳ/

#ከሚሴ
0921632606/ኑር አህመድ/
0915543171/ሁሴን/

#ሻሸመኔ
+251915596576/አሸናፊ/

#ቡታጅራ
0910899212/Yab/

#ጅማ
+251942630419/ፍላጎት/
0911670454/አሰፋ/

•ከ1ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ የመደበኛ የመማሪያ እና አጋዥ መፅሃፍትን በመለገስ ለመጭው ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን እናውርስ!!

📚የዘንድሮው አመት ተፈታኝ ተማሪዎች እና ወላጆች በዚህ ስራ ላይ በስፋት በመሳተፍ ለመጭው ትውልድ አርዓያ ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን!

5ኛው አመት የTIKVAH-ETHIOPIA የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ!

በዚህ ሀገራዊ ስራ መሳተፍ የምትፈልጉ የበጎ አድራጎት #ማህበራትና #ግለሰቦች @tsegabwolde

በሁሉም ከተሞች ያሉ አስተባባሪዎችን በየዕለቱ እናውቃለን!

📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚

ትግራይ ክልል #ኢሮብ አካባቢ የምትገኙ የቤተሰባችን አባላት መልዕክት አስቀምጡልን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እሁድን በበጎ ተግባር!

#አዲስ_አበባ

💫የአንድ እሽግ ለአንድ ልጅ የሙዚቃ ድግስ ነገ እሁድ ነሃሴ 26 በጌትፋም ሆቴል ይደረጋል። መግቢያ: 12 ደብተር - 2 እስክርቢቶ - 2 እርሳስ - 2 መቅረጫ እና 2 ላጲስ - የTIKVAH-ETH የአ/አ ቤተሰቦች እንዳትቀሩ! #onepackforonechild

💫Rotaract Ethiopia በጎ ስራ ላይ የተሰማራ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ሲሆን ለአዲሱ አመት #አልባሳት እያሰባሰበ ነው እናተም ተሳተፉ ያላችሁበት መጥተው ይወስዳሉ ደውሉላቸው Rotaract club of Atrons President Yeabsera --- +251922175164. (Or Natnael -@Natysf +251923594536, Sofonias - @SophoDarik +251 92 453 9140

#ወላይታ_ሶዶ

💫"አለን ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ማህበር ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ" ላለፉት ሁለት ቀናት ለ800 ተማሪዎች ለትምህርት የሚሆናቸውን ቁሳቁስ እያሰባሰበ ነው። በተጨማሪ የደም ልገሳ እየተደረገ ይገኛል። ነገም ለ3ኛ ቀን ይቀጥላል። ወላይታ ሶዶ ያላችሁ የTIKVAH-ETH ተከታዮችም እሁዳችሁን ከነሱ ጋር ማሳለፍ ትችላላችሁ። ስልክ +251913776084፣ 0926172318

#ሻሸመኔ

💫የሻሸመኔ ወጣቶች ነገ የይደግ በጎ አድራጎት ማእከልን ይጎበኛሉ እንዲሁም ግቢውን ያፀዳሉ። የሻሸመኔ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች ኑ እሁድን በመልካም ስራ እናሳልፍ ከሰአት 8:00 ሰአት ላይ CDI እንገናኝ ብለዋችኃል!! ስልክ፦0926940304

#ለኩ
💫በለኩ ከተማ የሚገኙ "እኔም ለወገን" የበጎ አድራጎት ማህበር አባላት የሻይ ቡና ፕሮግራም አዘጋጅተዋል። የለኩ ቤተሰቦቻችን እሁድን አብራችሁ!0986241726

💫"ነገ በለኩ ፉርቃን የአበባ እና የችግኝ መተከል ስነ ስርአት ስለሚኖረን የቻላችሁ ከጥዋቱ 3 ሰአት በለኩ ፉርቃን ግቢ በመገኘት አሻራችሁን እንድታሳርፉ ጀመአችን ጥሪውን ያስተላልፋል" ቢላል የለኩ ሙስሊም በጎ አድራጎት ጀመአ

#ድሬዳዋ

💫"የድሬዳዋ ስካውት ካውንስል አባላት ነን በከተማችን የሚገኙ መንገዶች በግራና በቀኝ ያሉ ጠርዞችን ነጭ እና ጥቁር ቀለም በመቀባት ለመንገዱ ውበት እንዲሁም በምሽት ለአሽከርካሪዎች በቀላሉ እንዲታይ በማድረግ የትራፊክ አደጋን ከመቀነስ አንፃር የበኩላችንን እየተወጣን ነው ። ስራው ገና አልተጠናቀቀም ነገም እለተ ሰንበት ይቀጥላል።"

#ወሊሶ

💫ወገኔን ለማስተማር እሮጣለሁ በከተማችን ቅን ወጣቶች የተቋቋመው የ" we are one" የበጎ አድራጎት ማህበር ባሳለፍነው አመት "ወገኔን ለማስተማር እኔም እሮጣለሁ" በሚል መሪ ቃል ታላቅ የእሩጫ ዉድድር ማሰናዳቱ የሚታወስ ነዉ። በዘንድሮ አመትም በተመሳሳይ መሪ ቃል በአይነቱ ልዩ በሆነ ሩጫ ዝግጅቱን አጠናቆ እርሶን እየጠበቀ ይገኛል ታድያ እርሶም የሩጫ ቲሸርት በመግዛት ከአላማችን ጎን ይሰለፉ። የቲሸርቱ ዋጋ 100 ብር የቲሸርቱ መገኛ ቦታ: ፓስታ ቤት፣የኛ ህንፃ ፣ክርኪስ እናም ሁሉም ቦታ አዙረው በመሸጥ ላይ ከሚገኙ አባላቶች

በሌሎች አካባቢዎች ያሉ እንቅስቃሴዎችን እንደደረሰኝ አቀርባለሁ!
በድጋሚ የጥንቃቄ መልዕክት!

የወደቀውን ዋርካ ለማንሳት ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ቢገኝም እስካሁን ማንሳት አልተቻለም፤ በመሆኑም ወደ ሀዋሳ መስመር እያሽከረከራችሁ የምትገኙ ከፍተኛ ጥንቃቄ አድርጉ። አደጋው በሰው ላይ እና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።

#ሻሸመኔ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሻሸመኔ

የኦሮሚያ ክልል 114 ባለ 75 ፈረስ ጉልበት ትራክተሮችን ለ114 ኢንተርፕራይዞች አስረከበ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳዳር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በምዕራብ አርሲ ዞን ሻሸመኔ ከተማ በተከናወነ ስነ ስርዓት ላይ ተገኝተው የትራክተሮቹን ቁልፍ ለኢንተርፕራይዞቹ አስረክበዋል።

አቶ ሽመልስ በዚሁ ፕሮግራም ላይ ባደረጉት ንግግር በክልሉ የሚደረገው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ አስተማማኝ እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል። አርሶ አደሩ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ወደ ሜካናይዜሽን እንዲገባ ለማድረግ በርካታ ስራዎች እንደሚከናወኑም ነው የተናገሩት።

በቅርብ ጊዚያትም በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ከውጭ የግብርና ማሽነሪዎችን ለማስገባት እየተሰራ እንደሆነም አንስተዋል። ምክትል ርዕሰ መስተዳደሩ የኬኛ ግብርና መሳሪያዎች ማምረቻ ፋብሪካንም ጎብኝተዋል።

ፋብሪካው በዚህ ዓመት 2 ሺህ ትራክተሮችን ለመገጣጠም እየሰራ እንደሆነም ነው በዚሁ ወቅት የተገለፀው። ከዚህ ቀደም ስራ አጥ የነበሩ 500 ወጣቶች ተደራጅተው በክላስተር ያረሱትን የ83 ሄክታር መሬት የቢራ ገብስ እርሻንም ምክትል ርእሰ መስተዳድሩ ጎብኝተዋል።

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ሻሸመኔ | የትራንስፖርት እንቅስቃሴው ተጀምሯል። መንገድ ላይ የነበሩ ድንጋዮችም እየተነሱ ነው። የንግድ ሰዎችም ወደ ስራቸው እንዲመለሱ መልዕክት እየተላለፈላቸው ይገኛል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሻሸመኔ

በሻሸመኔ ከተማ የሚገኘው ኢንስፓየር የልማት እና የመረዳጃ ማህበር "ህይወት ለ ህይወት" በሚል መሪ ቃል ለ 5ኛ ዙር ከሻሸመኔ ደም ባንክ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የደም ልገሳ ፕሮግራም ከ120 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ደም ለግሰዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሻሸመኔ

ዛሬ በሻሸመኔ ከተማ ቆሻሻ ውስጥ ተጥሎ የነበረ ቦምብ ፈንድቶ ያገለገሉ ፕላስቲኮችን እየለቀሙ የሚተዳደሩ አራት ልጆች ህይወታቸው አለፈ፡፡

ልጆቹ ያገለገሉ ፕላስቲኮችን እየለቀሙ ባለበት ሰዓት ከተጠራቀመ ቆሻሻ ውስጥ ቦምቡ መፈንዳቱን ፖሊስ ገልጿል።

በዚህም የአራት ልጆች ህይወታቸው ሲያልፍ፥ ሁለት ህፃናት ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

Via OBN / FBC

@tikvahethiopia