TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሀረር

በሐረር ከተማ #ከአራተኛ እስከ #ሐማሬሳ የጎዳና ላይ ጽዳት ዘመቻ ተካሄደ። በክልሉ ፍትህና ጸጥታ ጉዳይ ቢሮ አስተባባሪነት በክልሉ የሚገኙ የጸጥታ ሀይሎች የሀገር መከላከያ፣ የክልሉ ፖሊስ፣ የፌደራል ፖሊስ፣ የሚኒሻ አባላት፣ የማረሚያ ኮሚሽን፣ ቄሮ፣ ቀሬ፣ የክልሉ ወጣቶች እና የሀይማኖት አባቶች በጋራ በመሆን በዛሬው እለት ከጥዋቱ 12 ጀምሮ ከአራተኛ እስከ ሐማሬሳ የጎዳና ላይ የጽዳት ዘመቻ ተካሂዷል። የክልሉ ፍትህና ጸጥታ ጉዳይ ቢሮ እንደገለጸው ሐረር ከተማ ለነዋሪዎቻ ምቹ ከተማ እንድትሆን ብልሹ አመለካከትና አሰራርን ከክልሉ እናስወገድ በሚል መሪ ቃል የጽዳት ዘመቻው እንደተካሄደ ተገልጿል። ቢሮው እንደገለጸው በሌሎች አካባቢዎች ተመሳሳይ የጽዳት ዘመቻ እንደሚካሄድ ገልጾ የክልሉ ህብረተሰብ አካባቢውን ማጽዳት እንደሚጠበቅበት ገልጻል።

Via #AD
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AD

ፋና የወይባ ጡሽ የተመሰረተበትን  22ኛ አመት በአሉንና 4ኛ ቅርንጫፉ የመክፈቻ ስርአት አካሄደ።

በወ/ሮ ፋና ገ/መድህን ከ22 አመት በፊት የተመሰረተው ‘ ፋና የወይባ ጡሽ ’ በደንበኞቹ ዘንድ ያተረፈውን መልካም ስም እና ዝም በመጠበቅ ለአመታት መዝለቅ የቻለ ነው።

በአዲስ አበባ ሳር ቤት ደቡብ አፍሪካ ኤምባሲ ገባ ብሎ ካለው የመጀመርያ ቅርንጫፍ በተጨማሪ ቦሌ ከዮድ አቢሲኒያ ፊት ለፊት ፣ በመቐለ ሐውልቲ ፕላኔት ሆቴል ፊት ለፊት እንዲሁም 4ኛ ቅርንጫፉን ሲኤምሲ መሪ አካባቢ ለደንበኞች በሚመች አማካይ ቦታዎች ቅርንጫፎችን በመክፈት አገልግሎቱን አስፋፍቷል።

ቅዳሜ መስከረም 11 ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ሀገራዊ በሆነ ግብአት የ22 አመታት አገልግሎት የሰጠው 'ፋና የወይባ ጡሽ ፦
- የበርካቶች የማህፀንና የወገብ ጤና የተመለሰበት ፤
- የቆዳቸው ውበት የተጠበቀበት ፤
- በኑሮ ውጣ ውረድ የደከመ ሰውነታቸው  ዘና ያለበት መሆኑ በደንበኞች ተመስክሮለታል ተብሏል።

ወይባ ፤ ቦለቂያ ፤ ጡሽ እና የመሳሰለው አካባቢያዊ መጠሪያና ስያሜ ተሰጥቶት በተለያዩ የሃገራችን አከባቢዎች ጤናንና ውበትን ለመጠበቅና ለመንከባከብ ከትውልድ ትውልድ እየተላለፉ በመጡ እና ረጅም ዘመን በዘለቁ ማኅበረሰባዊ እውቀቶች ተፈጥሯዊ የሆኑ እጽዋቶችን የመጠቀም
የቆየ ባህላዊ ሥርዐትና ወግ አላቸው።

ይህን የቆየ ሀገረሰባዊ እውቀት ወደ ከተማ በማምጣት ፣ በማስተዋወቅና ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት በመስጠት 'ፋና የወይባ ጡሽ ' ላበረከተው አስተዋፅኦ '' የባህል ጥበባት ለማህበረሰብ ትስስርና ለሀገረ‐መንግስት ግንባታ " በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ በተካሄደው ሀገር አቀፍ የባህል ፌስቲቫል፣ ኤግዚቢሽን እና የኪነ-ጥበብ ስነ-ጥበብ ፈጠራ ውድድር እና ትዕይንት ላይ በላቀ ደረጃ ሰኔ 2016 ተሸላሚ ሲሆን ሌሎች ሽልማቶችንም አግኝቷል።

በእለቱ የፋና ወይባ ጡሽ አጀማመርና  ስለአገልግሎት አሰጣጡ የተዘጋጀ መፅሄት ይፋ ተደርጓል።

@tikvahethiopia