TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል‼️

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ካማሺ ዞን 4 ወረዳዎች ከ100 ሺህ በላይ ሰዎች አስቸኳይ #የምግብ_እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ተባለ፡፡

በዞኑ በሎጂጋንፎ፣ ያሶ አጋሎ ሜጢና ካማሺ ወረዳ ለሚገኙት ተረጂዎች በፀጥታ ስጋት ምግብ ለማቅረብ አለመቻሉን ተሰምቷል፡፡

የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ #ገርቢ_ሎላሳ ዛሬ ለሸገር ራድዮ ሲናገሩ ታጣቂዎች አሁንም መንገዱን #ስለዘጉት የእርዳታ እህል ለማቅረብ አዳጋች ሆኗል ብለዋል፡፡

ባሳለፍነው ቅዳሜ በመከላከያ ሰራዊት ታጅቦ የእርዳታ እህል ወደ ዞኑ ያደረሰ መኪና በመመለስ ላይ ሳለ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ 2 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ቆስለዋል ብለዋል አቶ ገርቢ፡፡

መንግስት ታጣቂዎቹን በመከላከልና መንገዱን በማስከፈት በአፋጣኝ የእርዳታ እህል ማቅረብ እንዲችል የዞኑ አስተዳዳሪ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ምንጭ፦ ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia