TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
Congratulations !

የተለያዩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዛሬ ተማሪዎቻቸውን አስመርቀዋል።

#ወላይታ_ሶዶ_ዩኒቨርሲቲ

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 5 ሺህ 726 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ዛሬ ለ13ኛ ጊዜ ባካሄደው የተማሪዎች ምረቃ ሥነ ስርዐት 5 ሺህ 726 ተማሪዎችን በመጀመሪያ፣ 2ኛ እና 3ኛ ዲግሪ አስመርቋል።

ከተመራቂዎቹ 448ቱ በ2ኛ ዲግሪ እንዲሁም ሰባቱ በ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ሲሆኑ ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 2 ሺህ 31ዱ ሴቶች ናቸው።

#ወራቤ_ዩኒቨርሲቲ

ወራቤ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 132 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው፡፡

#ኦዳቡልቱም_ዩኒቨርሲቲ

ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 354 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

ዛሬ ዩኒቨርሲቲው ባካሄደው 3ኛ ዙር የምረቃ ስነስርዐት የተመረቁ ተማሪዎች፤ በመደበኛ፣ በኤክስቴንሽን እና በቅዳሜና እሁድ መርሃ ግብሮች ስልጠናቸውን የተከታተሉ ናቸው።

#ሰላሌ_ዩኒቨርሲቲ

ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 54 ተማሪዎች አስመርቋል።

3ኛ ዙር ተመራቂዎቹ በዩኒቨርሲቲው አራት ኮሌጆች በመጀመሪያ ዲግሪ በመደበኛና ኤክስቴንሽን መርሃ ግብሮች ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ናቸው። ዛሬ ከተመረቁት ተማሪዎች 428ቱ ሴቶች ናቸው።

በሌላ በኩል ፦

የተለያዩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች አስመርቀዋል።

ጌጅ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ፣ ኩዊንስ ኮሌጅ፣ ግሬት ኮሌጅና ኤልኤም ኢንተርናሽናል የሆቴልና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ተቋማት ያስተማሯቸውን ተማሪዎች አስመርቀዋል።

Source : @tikvahuniversity