TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በኦሮሚያ ክልል ውስጥ #በሚገኝ አንድ የኢንዱስትሪ መንደር በሰባት የቻይና ዜጎች ላይ በተፈፀመ የዘራፊዎች ጥቃት አንድ ቻይናዊ መገደሉንና ሌላ አንድ መቁሰሉን የቻይና ኤምባሲን ጠቅሶ ሲጂቲኤን ዘግቧል፡፡

በጉዳዩ ላይ የአዳማ ከተማ ከንቲባ አቶ #አሰግድ_ጌታቸው እሁድ ቻይናውያን ላይ ደረሰ ስለተባለው አደጋ ለጋዜጠኛ #ኤልያስ_መሰረት ይህን ብለዋል፦ "ድርጊቱ የተፈፀመው አዳማ ኢንደስትሪ ፓርክ አቅራቢያ እሁድ አንድ ሰአት ገደማ ነው። እራት ከበሉ በሁዋላ በግሩፕ ወጡ። የሄዱበት ቦታ ከፓርኩ ሶስት ኪ.ሜ ርቀት ላይ ያለ ሲሆን ጭለማ እና ገደላማ ስፍራ ነው። የአካባቢው ሰው እንኳን አይሄድበትም። ለምን ወደዛ እንደሄዱ ገና እየተጣራ ነው። ከዛም ቻይናዎቹ እርስ በርስ እንደተወጋጉ ሟቹ ህይወቱ ከማለፉ በፊት ተናግሮ ነበር። ከዛ በሁዋላ ግን ሌሎች ሰዎች እንዳረጉት ለማስመሰል ተሞክሯል። በጥርጣሬ የተወሰኑ ቻይናውያንም፣ የአካባቢ ሰዎችም ተይዘዋል። ዝርፊያ ስለተባለው ግን አላውቅም እነሱም ተዘረፍን ብለው ሪፖርት አላደረጉም።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia