TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሞንቴኔግሮ ከኮቪድ-19 ነፃ መሆኗን አሳውቃለች!

ሞንቴኔግሮ ከኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) #ነፃ መሆኗን በትላንትናው ዕለት አሳውቃለች። በአጠቃላይ 324 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተይዘው የ9 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 315 ሰዎች አገግመዋል።

ምንም እንኳን ሞንቴኔግሮ ከኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ነፃ ብትሆንም የቫይረሱ ስርጭት ዳግም እንዳያገረሽ የሚወሰዱ የጥንቃቄ እርምጃዎች እንደሚቀጥሉ የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪ ሀገሪቱ ከግንቦት 24 ጀምሮ ያወጣችውን መስፈርት ለሚያሟሉ የአውሮፓ ሀገራት ዜጎች #ድንበሯን ለመክፈት እየተዘጋጀች እንደሆነ ተሰምቷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 129 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ! ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5,500 የላብራቶሪ ምርመራ አንድ መቶ ሃያ ዘጠኝ (129) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 1934 ደርሷል፡፡ ቫይረሱ የተገኘባቸው 75 ወንድ እና 54 ሴት ሲሆኑ የዕድሜ ክልላቸው ከ1 እስከ 90 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት…
#TikvahEthiopia #AtoKanGalwak

በጋምቤላ ክልል የተመዘገበው የመጀመሪያው ኬዝ !

የጋምቤላ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ካን ጋልዋክ ዛሬ በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠው ግለሰብ የ28 ዓመት እድሜ ያለው ደቡብ ሱዳናዊ መሆኑን ነገረውናል።

ድንበር ከተዘጋ በኃላ ደንበሩን አቋርጦ ወደ ጋምቤላ ክልል የገባና በለይቶ ማቆያ ውስጥ የነበረ ነው።

ግለሰቡ ወደ ማቆያ እንዲገባ የተደረገው የዛሬ ሁለት ሳምንት ሲሆን በተደረገለት ምርመራ በቫይረሱ መያዙ ተረጋግጧል። ወደ ህክምና ማዕከልም እንዲገባ ተደርጓል።

ከእሱ በተጨማሪ ወንድሙ አብሮት በለይቶ ማቆያ ውስጥ የነበረ ሲሆን በተደረገለት ምርመራ ከቫይረሱ #ነፃ መሆኑ ተረጋግጧል።

በቫይረሱ የተያዘው ግለሰብ ደንበር በማቋረጥ ተደጋጋሚ ምልልሶች የነበሩት ሲሆን ከእሱ ጋር ንክኪ ያላቸው ሰዎችን ወደ ኳራንቲን ለማስገባት እየተሰራ ይገኛል።

#TikvahEthiopia
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

የቀድሞው ጠ/ሚ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የደህንነት ኃላፊ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አቶ ኃይለማርያም እና ቤተሰባቸው ምርመራ እስኪደረግላቸው እራሳቸውን አግልለው የቆዩ ሲሆን የምርመራ ውጤታቸው #ነፃ መሆኑን በይፋዊ የትዊተር ገፃቸው አሳውቀዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FDREDefenseForce

በሶማሊያ አሚሶም ሰላም ማስከበር የሴክተር ሶስት 6ኛው ዙር የሠላም አስከባሪ ዘማቾች በአዲሱ የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ግንባታ ስትራቴጅ እና የሰራዊት ግንባታ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ሂሳዊ እይታ በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ውውይት አካሂደዋል።

በውይይቱ ወቅት የሴክተር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጄነራል አለሙ አየነ ሠራዊቱ የህገ-መንግስቱ ጠባቂና የዜጎች ሃብት እንጂ መንግስታት እና ፓርቲዎች በተቀያየሩ ቁጥር የሚቀያየር እና የሚበተን ሃይል እንዳልሆነ ገልፀዋል። ሰራዊቱ በፖለቲካ ፓርቲዎች እና በድርጅቶች በሚራመዱ አስተሳሰቦች ሰለባ እንዳይሆንም መጠንቀቅ እንዳለበት አስገንዝበዋል።

እኛ እንደ ሰራዊት የድርጅቶችና የፓርቲዎች ርዮት አለም ሃሳብ ተሸካሚዎችና አራማጆች ሳንሆን ፣ ከማንኛውም ፖለቲካ ድርጅት #ነፃ በመሆን በህገ መንግስቱ መሰረት በህዝብ ተመርጦ ወደ ስልጣን የመጣን ሃይል የማክበርና የመደገፍ እንጂ በሃይል መሳሪያ ታጥቆ ህገ መንግስቱን ለማፍረስ እና አገርን ስጋት ላይ የሚጥል ሃይል ካለ ተቀባይነት የለውም ሲሉ አሳስበዋል።

ምንጭ፦ የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ትላንት የፌስቡክ ፣ ዋትስአፕ፣ ኢንስታግራምና ሜሴንጀር መቋረጥ ለሌሎች ተመሳሳይ አይነት አገልግሎት ለሚሰጡ መተግበሪያዎች ትልቅ በር ከፍቶ ነው ያለፈው።

ትዊትር በትላንትናው ዕለት በአንድ ጊዜ ከፍተኛ የሆነ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች አስመዝግቧል።

ዛሬ ምሽት የቴሌግራም መስራች እንዲሁም ዋና ስራ አስኪያጅ ፓቬል ዱሮቭ ይፋ ባደረጉት መረጃ ፥ በአንድ ቀን ብቻ ከሌሎች ፕላትፎርሞች 70 ሚሊዮን አዳዲስ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች ተመዝግበዋል።

ፓቬል ዱሮቭ ፤ አዳዲስ የቴሌግራም ተጠቃሚዎችን "ወደ ትልቁ #ነፃ የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ወደ #ቴሌግራም እንኳን በደህና መጡ" ብለዋል።

@tikvahethiopia
#ነፃ_ዋይፋይ

ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ከተማ በመስቀል አደባባይ ፣ እንጦጦ ፣ አንድነት ፓርክ እና የወዳጅነት አደባባዮች በከፍተኛ ወጪ የዋይፋይ (WiFi) አገልግሎት ገንብቶ በነጻ ማቅረቡን ዛሬ ገልጿል።

@tikvahethiopia
#ነፃ_ጥቅል_ከኢትዮ_ቴሌኮም !

ኢትዮ ቴሌኮም በ2014 በጀት አመት 61.3 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

ይህም የእቅዱን 87.6 በመቶ ነው ብሏል።

ይህን በማስመልከት ለሦስት ቀናት የሚቆይ ነጻ ጥቅል ስጦታ ማቅረቡን ገልጿል።

ኢትዮ ቴሌኮም ያስመዘገበውን ስኬት አስመልክቶ ከህብረተሰቡ ጋር ለመጋራት ሲል የዳታ፣ ድምፅ እና የመልዕክት ጥቅል ስጦታዎችን ማቅረቡን ነው ዛሬ ያሳወቀው።

በዚህም፦

👉 1.5 ጌጋባይት ዳታ በቀን 512 ሜባ፤

👉 45 ደቂቃ በቀን 15 ደቂቃ፤

👉 100 መልዕክት በቀን 33 መልዕክቶችን፤

👉 የ10 ደቂቃ አለምአቀፍ ጥሪ በቀን 3 ደቂቃ ለተጠቃሚዎች በነጻ አቅርቧል።

(ማስታወሻ ፦ ዓለም አቀፍ የጥሪ ስጦታው የተበረከተው ያልተገደበ የድምጽ ጥቅል፣ የጹሑፍና የኢንተርኔት ለሚጠቀሙ ነው)

ስጦታው ከዛሬ ሐምሌ 21 ከሌሊቱ 06:00 ሰአት - እስከ ምሽቱ 12 ሰአት ድረስ ለ3 ቀናት ይቆያል።

@tikvahethmagazine
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ በአዲሱ ረቂቅ የትምህርት እና ጥናት ፖሊሲ ከቅድመ አንደኛ እስከ ስምንተኛ ከፍል የሚሰጥ ትምህርት #ነፃ እና #አስገዳጅ እንደሚሆን አስታውቋል።

በሚኒስቴሩ የስርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ ክፍል ኃላፊ ዶ/ር ቴዎድሮስ ሸዋረገድ ለኢቢሲ በሰጡት ቃል " በአዲሱ የትምህርት ፍኖታ ካርታ ግኝት መሰረት ዜጎች ከቅድመ አንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል በግዴታ እንዲማሩ ለማስቻልና የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱን የተሳለጠ ለማድረግ አጠቃላይ የትምህርት ረቂቅ አዋጅ ተግባራዊ ይደረጋል " ብለዋል።

ፍኖተ ካርታውን ለማዘጋጀት ሲሞከር የትምህርት ዘርፉ ያለበትን ሁኔታ ሊያሳይ የሚያስችል ጥናት መደረጉን ገልፀው መንግስት ለትምህርት ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና ጥራት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት በአዲስ መልክ ፍኖተ ካርታ አዘጋጅቶ ወደ ትግበራ ገብቷል ሲሉ አስረድተዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ : https://telegra.ph/MoE-08-16 (ኢቢሲ)

@tikvahethiopia
* የታክስ ማሻሻያ

ገንዘብ ሚኒስቴር የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ኢንቨስትመንትንና አስመጪዎችን የሚያበረታታ እንዲሁም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ የታክስ ማሻሻያ ተግባራዊ መደረጉን አሳወቀ።

ከውጭ የሚገቡ ሆነ ሀገር ውስጥ የሚመረቱ የኤሌክትሪክ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች፣ የቤት አውቶሞቢሎችና የእቃ መጫኛ ተሽከርካሪዎች ላይ ዝቅተኛ የጉምሩክ ታሪፍ የሚጣልባቸው ሲሆን ከተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ከኤክሳይዝ ታክስና ከሱር ታክስ #ነፃ እንደሚደረጉ ታውቋል፡፡

የታክስ ማሻሻያው አላማ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣውን የተሽከርካሪዎች ቁጥር በፖሊሲ ማዕቀፍ ከአካባቢ ደህንነት ጋር የሚስማማ ለማድረግ፣ በህብረተሰቡ ጤና ላይ ጉዳት የማያስከትል፣ በአየር ንብረትና በብዝሃ ህይወት ላይ ተጽእኖ የማያሳርፍ እና ታዳሽ የኃይል ምንጮችን በአግባቡ የሚጠቀም የመጓጓዣ ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ ሲሆን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እንዲቀርቡ ለማስቻልም ነው፡፡

በታክስ ማሻሻያው መሰረት የኤሌክትሪክ የቤት አውቶሞቢሎችን በተመለከተ ሙሉ በሙሉ ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ አውቶሞቢሎች ከጉምሩክ ቀረጥ፣ ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡

በከፊል ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ የኤሌክትሪክ የቤት አውቶ ሞቢሎችን 5 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡

ሙሉ ለሙሉ ተገጣጥመው ያለቀላቸው የኤሌክትሪክ አውቶሞቢሎች ወደ ሀገር ሲገቡ ደግሞ 15 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ ተወስኗል፡፡

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ETHIOPIA

ከውጭ የሚገቡ ሆነ ሀገር ውስጥ የሚመረቱ #የኤሌክትሪክ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች፣ የቤት አውቶሞቢሎችና የእቃ መጫኛ ተሽከርካሪዎች ላይ ዝቅተኛ የጉምሩክ ታሪፍ የሚጣልባቸው ሲሆን ከተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ከኤክሳይዝ ታክስና ከሱር ታክስ #ነፃ መደረጋቸውን ገንዘብ ሚኒስቴር አሳውቋል።

የታክስ ማሻሻያው በርካታ ዓላማዎች ያሉት ሲሆን ከዓላማው አንዱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እንዲቀርቡ ለማስቻል ነው።

በታክስ ማሻሻያው መሰረት (የቤት አውቶሞቢሎች) ፦

1ኛ. ሙሉ በሙሉ ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ አውቶሞቢሎች ከጉምሩክ ቀረጥ፣ ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ #ሙሉ_በሙሉ_ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡

2ኛ. በከፊል ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ የኤሌክትሪክ የቤት አውቶ ሞቢሎችን 5 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ #ሙሉ_በሙሉ_ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡

3ኛ. ሙሉ ለሙሉ ተገጣጥመው ያለቀላቸው የኤሌክትሪክ አውቶሞቢሎች ወደ ሀገር ሲገቡ 15 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ #ሙሉ_በሙሉ_ነጻ እንዲሆኑ ተወስኗል፡፡

@tikvahethiopia