TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update 10ኛ እና 12ኛ ክፍልን በተመለከተ ከኤጀንሲው ሰዎች ጋር #በስልክ ለመገናኘት ጥረት እይደረኩ ነው የደረስኩበትን አሳውቃችኋለሁ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሼህ አላሙዲ‼️

"ሼህ አላሙዲ ወደ #አዲስ_አበባ ይምጡ፤ #ሳዑዲ ይቆዩ #አናውቅም"- ጠበቃቸው
.
.
ላለፈው አንድ ዓመት ከሁለት ወር በሳዑዲ አረቢያ በእስር ላይ የቆዩት ሼህ መሐመድ ሁሴን አላሙዲ ከእስር #መፈታታቸውን ጠበቃቸው ተናገሩ። ትውልደ ኢትዮጵያዊው ቱጃር ከእስር የተፈቱት ዛሬ ከሰዓት መሆኑን ጠበቃቸው አቶ ተካ አስፋው ለጀርመን ድምፅ ራድዮ ገልጸዋል።

አቶ ተካ ሼህ አላሙዲንን #በስልክ ባይነጋግሯቸውም ከወንድማቸው ጋር አብረው እንዳሉ #አረጋግጩያለሁ ብለዋል። “ዛሬ ተፈትተዋል። አሁን ከሪያድ ወደ ጅዳ እየሄዱ ነው፤ ወደ ቤታቸው ማለት ነው። አጠገባቸው ካለ ሰው ጋር ተገናኝተናል። አዲስ አበባ ይምጡ፣ እዚያው ይቆዩ የምናውቀው ነገር የለም። እኛ አሁን #በመፈታታቸው ብቻ ደስታ ላይ ነው ያለነው።”

ሼህ መሐመድ ሁሴን አላሙዲ የሳዑዲ አረቢያ መንግስት በከፈተው የጸረ-ሙስና ዘመቻ ከሌሎች ቱጃሮች፣ ልዑላን፣ ሚኒስትሮች እና ባለስልጣናት ጋር በጥቅምት ወር 2010 ዓ. ም. ነበር በቁጥጥር ስር የዋሉት። ከእርሳቸው ጋር ታስረው የነበሩ ቢሊየነሩ ልዑል አልዋሊድ ቢን ታላልን ጨምሮ ሌሎች ተጠርጣሪዎች ከሳዑዲ አረቢያ መንግስት ጋር ድርድር ካደረጉ በኋላ እንደተፈቱ ሲገለጽ ቆይቷል። ሼህ አላሙዲ ስለተፈቱበት ሂደት የተጠየቁት ጠበቃቸው “ዝርዝሩን አላወቅንም። እኛ የምናውቀው መፈታታቸውን ብቻ ነው” ሲሉ ለጀርመን ድምፅ ራድዮ ምላሽ ሰጥተዋል።

ሳዑዲ አረቢያ በወጣቱ አልጋወራሽ ልዑል መሐመድ ቢን ሳልማን የሚመራ የጸረ-ሙስና ኮሚቴ ካቋቋመች በኋላ 11 ልዑላንን ጨምሮ 200 ገደማ ባለስልጣናት እና ነጋዴዎችን አስራ ነበር። ልዑላኑ እና ቱጃሮቹ ለመጀመሪያዎቹ ጥቂት ሳምንታት በሪያድ በሚገኝ ባለአምስት ኮከቡ ቅንጡ ሆቴል እንዲታሰሩ መደረጉ መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበር ይታወሳል። ተጠርጣሪዎቹ ሆቴሉን እንዲለቅቁ ከተደረጉ በኋላ በታሰሩበት ስፍራ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ይፈጸምባቸዋል የሚል ወቀሳ ሲሰማ ቆይቷል።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከ60 በላይ የጤና ባለሙያዎች ፤ " ጤና ሚኒስቴር በሕግ የተወሰነልንን ልዩ አበል አልከፈለንም " አሉ። የጤና ባለሙያዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት፤ የኮቪድ - 19 ወረርሽኝ መጋቢት 8 ቀን 2012 ዓ / ም መከሰቱን ተከትሎ የጤና ማኒስቴር ባወጣው ጥሪ መሠረት የኢፌደሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ግንቦት 18 ቀን 2012 ዓ / ም ባወጣው መመሪያ የሕክምና አገልግሎት ለሚሰጡ ለመላው ሀኪሞች በቀን…
#ጤና_ሚኒስቴር #ክስ

የፍርድ ቤት ውሳኔን በተደጋጋሚ ጣሰ የተባለው " ጤና ሚኒስቴር " ለ70 የጤና ባለሙያዎች የኮቪድ -19 ልዩ አበል እንዲከፍል ፍርድ ቤት በድጋሚ ለንግድ ባንክ ትዕዛዝ አስተላለፈበት።

70 የጤና ባለሙያዎች የኮቪድ ወረርሽኝ #ልዩ_አበል እንዲሰጣቸው በመሰረቱበት ክስ መሠረት ገንዘቡን እንዲከፍል ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሳኔ በተደጋጋሚ ጥሷል የተባለው " ጤና ሚኒስቴር " አሁንም ከንግድ ባንክ አካውንቱ #እየቆረጠ_እንዲከፍል ፍርድ ቤት በድጋሚ ለንግድ ባንክ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጤና ባለሙያዎቹ ገለጻና ከተጻፈው ደብዳቤ መረዳት ችሏል።

የጤና ባለሙያዎቹ ተወካይ የፍርድ ሂደቱ በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?

* ፍርድ ቤት ለባንክ ሲያዝ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው።

* የፋይናንስ ክፍሉ ኃላፊ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ድክመት ለፍርድ ቤት #ታስረው ቀርበው እንዲያስረዱ ቢታዘዝም ጉዳዩን እንዲያስፈፅም የታዘዘው የፌደራል ፖሊስ መስሪያ ቤቱ ድርስ በመሄድ ቢጠይቅም እረፍት እንደወጡና እስከ ሰኞ (ያለፈው ሳምንት ሰኞ) እንደሚመጡ አሳውቀው ነበር። ከዚያ በኋላም ፍርድ ቤት መጥተው አያውቁም።

* ታስረው እንዲቀርቡም #ከሁለት_ጊዜ_በላይ ነው የታዘዘው።

* ፍርድ ቤት በራሳቸው እንዲፈፅሙ ግን በተደጋጋሚ (ከአምስት ጊዜ በላይ) ትዛዝ ሰቶ ነበር።

* ሰዎቹ በፍፁም ለህግ ተገዢ አለመሆናቸውን እና እምቢተኝነታቸውን በተደጋጋሚ ጊዜ አሳይተውናል።

* ለፍርድ ቤት ውሳኔ ያላቸው ንቀት በቃላት የሚገለፅ አይደለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ይሄንን የጤና ባለሞያዎች መረጃ በማደራጀት ሂደት የጤና ሚኒስቴርን ምላሽ እና ማብራሪያ ለማካከት ብዙ ቢደክምም ምላሽ ሰጪ አላገኘም።

አሁንም #በአካልም ይሁን #በስልክ ምላሽ ሰጣለሁ የሚል የሚኒስቴር መ/ቤቱን አካል ለማስተናገድ ዝግጁ ነው።

ዝርዝሩን ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-14

የመረጃው ዝግጅት በአዲስ አበባ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia