TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ያማል---እጅግ በጣም ያማል‼️

በዚህ ሳምንት #የመን ርዕሠ-ከተማ #ሰነዓ ውስጥ በሁለት ትምሕርት ቤቶች አቅራቢያ በተጣለ #ቦምብ 14 ህጻናት መገደላቸዉን የተመድ #የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ አወገዘ።

የድርጅቱ የመካከለኛ ምሥራቅ እና የሰሜን አፍሪቃ ክፍል ሃላፊ ጊርት ካፔላሬ እንዳሉት ህጻናትን መግደል እና አካለቸዉን ማጉደል የህጻናትን መብቶች የሚጻረሩ እጅግ ከባድ ወንጀሎች ናቸው። እርምጃው ወላጆችም ልጆቻቸውን ወደ ትምሕርት ቤት እንዳይልኩ የሚያደርግ መሆኑን ጠቅሰዋል። በጥቃቱ ሌሎች 16 ተማሪዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል። አብዛናዎቹ እድሜያቸው ከ9 ዓመት በታች ነው። #ሰንአ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ ከሚደረግላቸው ክፉኛ ከተጎዱት ውስጥ በአስጊ ሁኔታ ላይ የሚገኙም እንዳሉ ገልጸዋል።

ባለፈው እሁድ የየመን አማጽያንን የሚወጋው ሳዑዲ መራሹ ህብረት ሰንአ ውስጥ በመኖሪያ አካባቢዎች ላይ ባካሄደው የአየር ድብደባ ቢያንስ 11 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን በኢራን ይደገፋሉ የሚባሉት የሁቲ አማጽያን ተናግረዋል። እንደ አማጽያኑ ከተገደሉት አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ናቸው።

Via የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia