TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን እያስመረቀ ይገኛል!

ጅማ ዩኒቨርስቲ በቅድመና በድህረ ምረቃ ዘርፎች ያስተማራቸውን 3 ሺህ 139 ተማሪዎች ዛሬ እያስመረቀ ነው። ከእነዚህ ምሩቃን ውስጥም 237 የህክምና ዶክተሮች፣ 27 የጥርስ ህክምና ዶክተሮች 8ቱ ደግሞ የሶስተኛ ድግሪ ተመራቂዎች ናቸው፡፡ ከተመራቂዎች መካከልም 13ቱ ከሶማሊላንድና ከሩዋንዳ የመጡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19 #ETHIOPIA

የዓለም ስጋት የሆነው የኮሮና ቫይረስ በሽታ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ለሚደረገው የመከላከል ሥራ ተጨማሪ ከ5 ሚሊየን በላይ የመተንፈሻ አካላት ጭንብሎች እንደሚገዙ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ET302

መጋቢት 1/2011 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲጓዝ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 ET302 ማክስ 8 አውሮፕላን የተከሰከበት ቦታ ላይ ዛሬ የሙት አመት መታሰቢያ ስነስርአት ተከናውኗል።

ስነስርአቱ የተዘጋጀው በአካባቢው ነዋሪዎች ሲሆን በሚልኪ የማስታወቂያ ስራዎች አስተባባሪነት የሚከናወን መሆኑን የሚልኪ አድቨርታይዚንግ ስራ አስኪያጅ አቶ ቀልቤሳ መገርሳ ተናግረዋል።

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ETH302

ለቦይንግ 737 አውሮፕላን ሰለባዎች ሙት አመት መታሰቢያ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ካህናት ጸሎት አድርገዋል። የአካባቢው ፈረሰኞች ዛሬ ለአመት የዘለቀው ሀዘን የሚያበቃበት ቀን መሆኑን ለማሣወቅ ጥቁር እና ነጭ ሰንደቅ አላማዎችን በመያዘ ተገኝተው ነበር። አባ ገዳዎችም ምስጋና አቅርበዋል።

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪዎችን የትራንስፖርት ችግር ለመፍታት በተያዘው በጀት ዓመት አንድ ሺ የሚሆኑ የግል ታክሲዎችን ለማስገባት መታቀዱን የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ባለሥልጣን አስታውቋል። በመንግሥት ሦስት ሺ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብሶችን ለማስገባት እየተሠራ መሆኑንም ተሰምቷል።

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ItsMyDam

ኢትዮጵያ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላትን አቋም ለማስረዳት በተለያዩ አገራት ከፍተኛ የልኡካን ቡድን በመላክ ላይ ትገኛለች።

በዚሁ መሰረት በኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ የተመራ ከፍተኛ የልኡካን ቡድን ዛሬ መጋቢት 3 ቀን 2012 ዓም ኬንያ ናይሮቢ በመገኘት ኢትዮጵያ በታላቁ የህዳሴው ግድብ ጋር በተያያዘ ያላትን ግልጽ አቋም ለፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ አስረድቷል።

ሁለቱ መሪዎች ከህዳሴው ግድብ ጋር በተያያዘ ያደረጉትን ውይይት ተከትሎም የጋራ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል።

በፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የሚመራው የልኡካን ቡድን በቀጣይም በሌሎቹ የአባይ ተፋሰስ አገራት ተመሳሳይ ጉብኝት በማድረግ ለአባል አገራቱ መሪዎች የኢትዮጵያን አቋም እንደሚያስረዳ ይጠበቃል።

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የመርካቶ የአውቶብስ ተርሚናል!

የመርካቶ የአውቶቡስ ተርሚናል ግንባታ በመፋጠን ላይ መሆኑን የትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል። የተርሚናሉ ግንባታ 84 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን፥ በ2012 በጀት አመት ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ርብርብ በመደረግ ላይ ነው፡፡

የአውቶቡስ ተርሚናሉ የተሳፋሪዎችን ምቾት በመጠበቀ በርካታ አገልግሎቶችን መስጠት ያስችላል፡፡ ተርሚናሉ በአንዴ ለ20 አውቶቡሶች አገልግሎት መስጠት የሚያስችል፤ የራሳቸው መግቢያ እና መውጫ ያላቸው ሁለት ወለሎችን አካቷል፡፡

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Attention

ተጓዳኝ ሕመም የሌለባቸውና በዕድሜ ወጣት የሆኑ ሰዎች በኮቪድ-19 ሕይወታቸው እያለፈ መሆኑን በሚሊኒየም የኮቪድ19 ሕክምና ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ውለታው ጫኔ አስታወቁ።

ቫይረሱ በራሱ ተጨማሪ ተጓዳኝ የጤና ችግሮችን እንደሚያስከትል አሳስበዋል።

ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ውለታው ፤ "የኮቪድ 19 ቫይረስ ተጓዳኝ ህመም ያለባቸውንና በዕድሜ የገፉትን ብቻ ነው የሚያጠቃው የሚለው የተሳሳተ ግንዛቤ አሁንም በስፋት ይስተዋላል። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የታየው ግን የተጠቁት ተጓዳኝ ህመም የሌለባቸው በ30ዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ጭምር ናቸው" ብለዋል።

ምንም ዓይነት ተጓዳኝ ህመም የሌለባቸውና በዕድሜ ወጣት የሆኑ ሰዎች በቫይረሱ ሕይወታቸው እያለፈ መሆኑን የጠቆሙት ዶክተሩ፣ ምናልባት በዕድሜ የገፉና ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው ላይ የበለጠ ቢከፋም እየሞቱ ያሉት ግን በሁሉም የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ዜጎች መሆናቸውን ገልፀዋል።

አሁን ላይ ባለው ሁኔታ የጽኑ ህሙማን ታካሚዎችና በኮቪድ-19 ሕይወታቸው የሚያልፍ ወገኖች ቁጥር ጨምሯል። የማሽን ድጋፍና ኦክስጅን የሚያስፈልጋቸው ታካሚዎች ቁጥር ከዕለት ወደ ዕለት እያደገ መምጣቱን አስታውቀዋል።

እንደዶ/ር ውለታው ገለፃ፤ ከወራት በፊት 60 % የሚሆኑ ታካሚዎች ቶሎ አገግመው የሚወጡ ታካሚዎች ነበሩ፤አሁን ላይ ግን ከ50 በመቶ በላይ ያለው ታካሚ በፀና ታሞ የሚመጣ ነው። ይህም የሚያሳየው መዘናጋት መኖሩንና ከውጭ ተጎድተው መቆየታቸውን ነው።

ጥንቃቄ በጎደለ ቁጥር የቫይረሱ ዝውውር እየሰፋ እንደሚሄድ ያመለከቱት ዶክተሩ ከሰዎች ጋር ሳይገናኙ በቤት ውስጥ የቆዩ እናቶችና አባቶች መዘናጋት በመኖሩ ምክንያት በቫይረሱ የመጠቃት ዕድላቸው እየጨመረ መጥቷል። ይህም የሞት ቁጥር እንዲጨምር ማድረጉን አመልክተዋል።~ #EPA

@tikvahethiopia
የተማሪዎችን ቅበላ እና ድልደላ የሚያስተዳድርበት ሥርዓት ማዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ አስታውቋል !

የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን ቅበላና ድልደላ የሚያስተዳድርበት ሥርዓት ማዘጋጅቱን ገልጿል።

የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ ዋና ዳይሬክተር ተሻለ በሬቻ ለኢፕድ እንደገለፁት፣ ዩንቨርሲቲው የተማሪዎችን ቅበላና ድልደላ የሚያስተዳድርበት ሥርዓት አዘጋጀቶ ለኢፊድሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንዲፀድቅ አቅርቧል።

በዚህም በቅርቡ ፀድቆ ዩንቨርሲቲው ተማሪዎችን መቀበል እንደሚጀምር ገልጿል።

እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ፤ ዩንቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን መቀበል የሚጀምር ሲሆን ተማሪዎቹ በኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ የሚሰጥ የመግብያ ፈተናም እንደሚሰጣቸው ገልፀዋል።

በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት ወር ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን ተቀብሎ በመጀመሪያ ዲግሪ እንደሚያስተምርም ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። #EPA

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የሀዋሳ ታቦር ተራራ በባለሃብቶች እንዲለማ ለማድረግ እየተሰራ ነው ተባለ።

የሀዋሳ ልዩ መለያ የሆነው 'ታቦር ተራራ' ባላሀብቶች መዋዕለ ነዋያቸውን የሚያፈሱበትና የኢንቨስትመንት የስበት አካል እንዲሆን እይተሰራ መሆኑን የከተማይቱ ም/ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ተናግረዋል።

ምክትል ከንቲባው፥ የታቦር ተራራ ባለሃብቶች እንዲያለሙትና "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክትን ሚስተካከል ልማት የሚከናወንበት ስፍራ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

ሀዋሳ የመላው ኢትዮጵውያን ከተማ ከመሆን አልፋ የቱሪስቶች መዳረሻ በመሆኗ ሰፊ የኢንቨስትመንት ሥራ በማከናወን ሀገርን ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

ምክትል ከንቲባው፥ ታቦር ተራራን ጨምሮ በሃዋሳ አቅራቢያ የሚገኙ ሃብቶችን ሥራ ላይ የማዋል ብርቱ ጥረት መጀመሩን ጠቁመው በቀጣይ ዘርፈ ብዙ ስራዎች እንደሚከናወኑ ገልፀዋል። #EPA

@tikvahethiopia